
“ጃዋር ሳይጠየቅ ፍትህ እናሰፍናለን ማለት ቀልድ ነው”
ዶክተር ስዩም መስፍን
የአዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል እና የሰላም ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ የሆኑት ዶክተር ስዩም መስፍን 78 ንጹሀን ዜጎች በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደሉ ምክንያት የሆነው አሸባሪው ጃዋር መሀመድ እና ግብረ አበሮቹ በህግ ሳይጠየቁ ሌሎችን በማሰር ፍትህ እናሰፍናለን ማለት ቀልድ ነው
ሲሉ አቃቤ ህግን ክፉኛ የተቹ ሲሆን “ጃዋርና ግብርአበሮቹ በህግ ባልተጠየቁበት ሀገርና ሁኔታ ስለ ህግ ማስከበር/መከበር ማንም ግለሰብ/የመንግስት ተቋም የመናገር ሞራል የለውም። በህግ የሚያስጠይቀው ቢያንስ ደግሞ ከሀገር የሚያስባርረው ብዙ ማስረጃዎች ያሉበት ወንጀለኛ በህግ አለመጠየቅ ፤ የአያሌ ንጹሀን ደም እንዲያፈስ ከመፍቀድ አይተናነስም።