እነ ዮሐንስ ዳንኤል አውሮፕላን በቁጥጥር ሥር በማዋልና አለመታዘዝ ወንጀል ተከሰሱ

ዜና እነ ዮሐንስ ዳንኤል አውሮፕላን በቁጥጥር ሥር በማዋልና አለመታዘዝ ወንጀል ተከሰሱ ታምሩ ጽጌ ቀን: September 15, 2024 በቅጽን ስሙ ጆን ዳንኤል በመባል፣ በማኅበራዊ ድረ ገጽ ሥራዎቹ የሚታወቀው ዮሐንስ ዳንኤልና ሌሎች አምስት ግለሰቦች፣ አውሮፕላንን ያላግባብ መያዝ (በቁጥጥር ሥር ማዋል፣ የመንግሥት ሠራተኛ ኦፌሴላዊ ግዴታ እንዳይፈጸም መቃወም፣ አለመታዘዝና መልካም ስምን የሚያጎድፍ ተንቀሳቃሽ ምሥል በኮምፒዩተር ሥርዓት አማካይነት ማሠራጨት ወንጀሎች […]

ጂቡቲ የታጁራ ወደብን በጋራ ለማስተዳደር እንጂ ለኢትዮጵያ አሳልፋ እንደማትሰጥ ገለጸች የጂቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

በዮሐንስ አንበርብር September 15, 2024 የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሞሐመድ አሊ ዩሱፍ  ኢትዮጵያ ታጁራ ወደብን በጋራ እያስተዳደረች እንድትጠቀምበት እንጂ ጠቅልላ እንድትወስደው ወይም እንድትገዛው የጂቡቲ መንግሥት ሐሳብ አለማቅረቡን የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ። የጂቡቲ መንግሥት በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ በማሰብ፣ ኢትዮጵያ የታጁራ ወደብን መቶ በመቶ በማስተዳደር እንድትጠቀምበት ምክረ ሐሳብ ማቅረቡን ለቢቢሲ የተናገሩት የጂቡቲ የውጭ […]

መንግሥት ፖታሽ ለማምረት ፈቃድ የወሰዱ ኩባንያዎች ሥራ ካልጀመሩ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀ

በበጋዜጣዉ ሪፓርተር September 15, 2024 የግብርና ማዳበሪያ በአገር ውስጥ ለማምረት መሠረታዊ ግብዓት የሆነውን ፖታሽ ለማውጣት ፈቃድ ወስደው ያለ ሥራ ለረዥም ጊዜ የተቀመጡ ኩባንያዎች በዚህ ዓመት (2017) ሥራ ካልጀመሩ፣ ሕጋዊ ዕርምጃ እንደሚወሰድባቸው መንግሥት አስጠነቀቀ፡፡ በአፋር ክልል የፖታሽ ማዕድን ለማምረት ፈቃድ ለወሰዱ ኩባንያዎች፣ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ መጻፉን የማዕድን ሚኒስቴር በሪፖርቱ ጠቅሷል፡፡ ከእነዚህ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው ትልልቅ የፖታሽ አልሚ ባለፈቃዶች […]

የደመወዝ ጭማሪ ብቻ ሳይሆን መነሻ ወለልም በአስቸኳይ እንዲስተካከል ተጠየቀ

በዳዊት ታዬ September 15, 2024 የኢሠማኮ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለመንግሥት ሠራተኞች የተደረገውን የደመወዝ ጭማሪ በአዎንታዊነት የሚቀበሉት ቢሆንም፣ በግል ሠራተኞችና ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች መነሻ የደመወዝ ወለል በአስቸኳይ መቀመጥ እንዳለበት፣ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ ኮንፌዴሬሽኑ ሰሞኑን ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ይህንኑ ጉዳይ አፅንኦት ሰጥቶ ውሳኔ ያሳለፈበት ሲሆን፣ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር በተያያዘ የሚፈጠሩ ጫናዎችን ለመቀነስ የደመወዝ […]

የዘረመል ቴክኖሎጂ መስፋፋት ለሆርቲካልቸር ዘርፍ ልማት ሥጋት መሆኑ ተገለጸ

በሔለን ተስፋዬ September 15, 2024 የዘረመል ቴክኖሎጂ መስፋፋቱና በጤና ላይ የሚያደርሰው አደጋ መበራከቱ፣ ለሆርቲካልቸር ዘርፍ ልማት ሥጋት መሆኑን፣ የግብርና ሚኒስቴር ያዘጋጀው የሆርቲካልቸር ልማት ግብይት ስትራቴጂ አመላከተ፡፡ ስትራቴጂው የተዘጋጀው ከ2016 እስከ 2025 ዓ.ም. ለመተግበር ሲሆን፣ የሆርቲካልቸር ዘርፍ እንዳያድግ ሥጋት ይሆናሉ ተብለው ከተዘረዘሩት መካከል የዘረመል ቴክኖሎጂ መስፋፋት መሆኑ ተገልጿል፡፡ ከዓለም አቀፉ የኃይል መቃወስ ጋር ተያይዞ የዘረመል ምርምርና […]