ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አባል ለመጀመሪያ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ

17 መጋቢት 2025, 15:55 EAT የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ቅዳሜ ዕለት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ያለመከሰስ መብታቸውን የተነሳው የምክር ቤት አባል አቶ ዮሃንስ ተሰማ፤ ከአንድ ሳምንት እስር በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ። አቶ ዮሃንስ የቀረቡበት የአሶሳ ዞን የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ በምክር ቤት አባሉ ላይ 14 የምርመራ ቀናትን መፍቀዱን ባለቤታቸው እና አንድ የፓርቲው […]

በኮንጎ ግጭት ምክንያት ሩዋንዳ ከቤልጂየም ጋር ያላትን ግንኙነት አቋረጠች

17 መጋቢት 2025, 18:00 EAT ሩዋንዳ ከቤልጂየም ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አቋረጠች። ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግጭት ጋር በተያያዘ ቤልጂየም ሩዋንዳን “በተደጋጋሚ አናንቃለች” በሚል ነው ሩዋንዳ ግንኙነቷን ለማቋረጥ የወሰነችው። ሩዋንዳ ለአማጺ ቡድኑ ኤም23 በምታደርገው ድጋፍ ምክንያት የአውሮፓ አገራት ማዕቀብ እንዲጥሉባት ቤልጄም ጥሪ ስታደርግ ቆይታለች። የቤልጂየም ዲፕሎማቶች ኪጋሊን ለቀው እንዲወጡ 48 ሰዓታት ተሰጥቷቸዋል። የቀድሞዋ ቅኝ ገዢ ቤልጄም […]

አሜሪካ በየመን በፈጸመችው አዲስ ጥቃት 53 ሰዎች መሞታቸውን የሁቲ አማፂያን ገለፁ

17 መጋቢት 2025, 14:52 EAT የየመን ሁቲ አማፂያን አሜሪካ በፈጸመችው አዲስ ጥቃት አምስት ሕጻናትን ጨምሮ 53 ሰዎች መሞታቸውን ገለፁ። አማፂ ቡድኑ ሰኞ ማለዳ በአል ጃኡፍ እና ሁዳይዳህ አካባቢዎች የሚገኙ ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን የገለፀ ሲሆን፣ የአሜሪካ ማዕከላዊ ኮማንድ በበኩሉ ጥቃት መፈጸሙ እንደቀጠለ መሆኑን ተናግሯል። አሜሪካ የሁቲ አማፂያን በቀይ ባሕር መርከቦች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት ለማስቆም የሚደረገው […]