ካናዳ ከትራምፕ ጋር የምትደራደረው “በራሷ ፍላጎቶች መሰረት” እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትር ካርኔይ ለቢቢሲ ተናገሩ

ከ 7 ሰአት በፊት የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ኮርኔይ አገራቸው ከአሜሪካ ተገቢው አክብሮት እንደሚገባት ገልፀው በንግድ እና ደኅነንነት ጉዳዮች ላይ ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ወደ ውይይት የሚገቡት “በራሳችን ፍላጎት መሰረት ነው” ብለዋል። ምርጫው ሲጠናቀቅ ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ላይ ካርኔይ ዋሽንግተን ለጉብኝት የሚሄዱት የካናዳን ሉዓላዊነት ያከበረ “ኮስተር ያለ ንግግር የሚኖር ከሆነ” ብቻ እንደሆነ አስታውቀዋል። እንደ ካናዳ […]

ትራምፕ 100 የሥልጣን ቀናቸውን ራሳቸውን በማወደስ እና ተቀናቃኞቻቸውን በመወረፍ እያከበሩ ነው

ከ 7 ሰአት በፊት የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሁለተኛ የሥራ ዘመን 100 ቀን የሥልጣን ቆይታቸውን የምርጫ ዘመቻ በመሰለ ንግግር ስኬቶቻቸውን ሲያወድሱ ጠላቶቻቸውን ደግሞ ወርፈዋል። “አብዮታዊ የጋራ አስተሳሰብ” ሲሉ በሚቺገን ግዛት ለተሰበሰቡ ደጋፊዎቻቸው ስኬታቸውን ያወደሱት ትራምፕ፤ ሥልጣናቸውን “ለጥልቅ ለውጥ” እየተጠቀሙበት እንደሆነ ተናግረዋል። “ገና መጀመራችን ነው። ገና ምን አይታችሁ” ሲሉ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ማክሰኞ ዕለት ተናግረዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ […]