ኤርትራዊያን በመቀሌ —የጋዜጠኛው የጉዞ ማስታወሻ (ነቢያት አማረ – ኢትዮጲስ ጋዜጣ)

01/02/2019 አዲስ አበባ መስከረም 20 ቀን ምሽት ሁለት ሰአት ላይ ነበር የመቀሌ በረራችን፡፡ እኔና የምሰራበት ቴሌቪዥን ጣቢያ ካሜራ ባለሙያ ከበረራችን አንድ ሰአት አስቀድመን ቦሌ አየር ማረፊያ ደርሰናል፡፡ አውሮፕላኑ ላይም ስንሳፈር ሰአታችንን እንደጠበቅን ነበር፡፡ ነገር ግን፣ አየር ማረፊያው በአየር ትራፊክ በመጨናነቁ የተነሳ፣ ከበረራ መነሻችን ለ 30 ደቂቃዎች ያክል ለመዘግየት ተገደድን፡፡ በመቶ ሺህ ብሮች የሚገመቱ ሁለት ካሜራዎችን […]

ትግራይና ኢትዮጵያ ሁለት አገራት? ወይስ አንድ አገር? (አንተነህ ሙሉጌታ)

01/02/2019 ይህንን ጥያቄ እንድጠይቅ ያረገኝ ሰሞኑን ኤርትራ በትግራይ በኩል ያለውን ድንበር ዘግታ ከኢትዮጵያ ጋር ግን በአፋር ክልል በቡሬ በኩል ያለውን ድንበር ክፍት አድርጋ የሁለቱ አገራት ዜጎች ያለምንም ችግር እየተጠቀሙበት ነው። ይህንን ተከትሎ ኤርትራ ድንበሩን የዘጋችው በኢትዮጵያ ላይ ነው ወይስ በትግራይ ላይ? በትግራይ ላይ ከዘጋችው በኢትዮጵያ ላይ እንደዘጋችው አይቆጠርም ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ነው። ኤርትራ ከኢትዮጵያ […]

“ትግራይ ትግርኚ” የምትባል አገር የመመስረት ክፉ ቅዠት!!! (ናትኤል አስመላሽ)

01/01/2019 መ/ር ገብረኪዳን እና ኤርትራዊው ተስፋጽዮን ህወሓት ከስልጣን መባረርዋ አይቀሬ መሆኑ ስታወቅ፣ የተንኮል አባት አቶ ስብሓት ነጋ፣ አግአዝያን የሚባል ድርጅት በድብቅ መስርተው ነበር። የዚህ ቡዱን ዋና ተልእኮ፣ ትግርኛ ተናጋሪ የትግራይ ተወላጆች እና የኤርትራ ተወላጆች አንድ አገር እንዲመሰረቱ እና ከፊል የኤርትራ መሬት እና የትግራይ መሬት ለሁለት በመሰንጠቅ፣ ትግራይ ትግርኚ የምትባል አገር መመስረት ነው። በትግራይ በኩል አድዋ፣ሽሬ፣አኽሱም፣ዓድግራት […]

ሕገ መንግሥት ተብዬው የወለደውን ሞትና መፈናቀል ጾምና ምሕላ በማወጅ መፍታት አይቻልም! (አቻምየለህ ታምሩ)

01/01/2019 በአገራችን ኢትዮጵያ ምሁራንና የሃይማኖት አባቶች እንደሚባሉት የኅብረተሰባችን ክፍሎች ከየመጣው ጋር አሰላለፉን የሚያስተካከልና የመንፈስ ደካማ የሆነ የኅብረተሰብ ክፍለ ያለ አይመስለኝም። ጥሊያን በአድዋ ጦርነት ድባቅ ተመትቶ ሽንፈት ከመከናነቡ ወራት በፊት ሸዋን እንዲወጋና ኢትዮጵያን ቅኝ እንዲይዝ እነ ባልዴሴራን በመስቀል ባርከው አምባላጌ ድረስ የሸኙት የአክሱሙ ንቡረእድ ናቸው። ከአርባ አመት በኋላም ፋሽስት ጥሊያንን ከበሮ እየመቱ ለመቀበል የሃይማኖት አባቶችን የቀደማቸው […]

ለአታላይ ስለማያመቹት የኢትዮጵያ ወሰን ፈጣሪ ወንዞችና ስለክልል የለሹ አማርኛ ተናጋሪ ጥቂት ነጥቦች (ከኤፍሬም የማነብርሐን (J.S.D.))

01/01/2019 ባለፉት 27 ዓመታት፣ ማለትም ኢትዮጵያን ከተቆጣጠረበት 1983 ዓመት ምህረት ጀምሮ፣ ወያኔ ኢትዮጵያን በትግራይ የበላይነት ቢያንስ ለመቶ ዓመታት ለመምራት የሚያስችለውን የወሰን አከላለልና የሕዝቦቿን የዜግነት መብት ለራሱ በሚያመቸው አኳኅን ብዛት ያለው ሕዝብ ያለተወከለበትን ሕገመንግስት ነድፎ፣ በሕዝቦቿ ላይ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈጸም ይህንን የክፋትና የጥፋት ዓላማ ለመተግበር ላይ ታች ሲል ከረመ። ለዚህም ዓላማ መሳካት የመጀመሪያ ዋና ኢላማ ያደረገው […]

አቶ ለማ መገርሳ ታፍኖ የቆየውን የመከራ ምስጢር ይፋ አወጡ!!! (ጋዜጠኛ እሸቱ ገለቱ)

01/01/2019 “… ዶ/ር አብይ ኦሮሞ በመሆኑ ከቤተመንግስት በጉልበት እሳት አቀጣጥለን እናስወጣዋለን የሚሉ ከመጡ እንሟሟታታለን እንጂ አይለቅም!!!” አቶ ለማ መገርሳ “ከሰማይ በታች የሚፈሩ ነበር – ለመናገር አይደለም ቀና ብለን የማናያቸው ነበሩ ባለጊዜዎቹ፡፡ በዚህ ሀገር ለጥቂቶች ህግ የበታች ሆኖ ቆይቷል፡፡ ከ17 ቀናቱ በፊት 700 ቀናት ነበሩ፡፡ አንድ ቀን ታሪክ ያወጣዋል፡፡ ላለፉት 7 አመታት ስንሳደድ ነበር፡፡ ከስልጣንም የተባረርን […]

መቀሌ ሀገር ሆናለች! – በውድቀት ዋዜማ ላይም ትገኛለች!!! (አዲስ ፋሽን መጽሄት)

01/01/2019 በፖለቲካ እይታ ገና ወደ መቀሌ ስትገባ አስጨናቂ ፍተሻ ይጠብቅሀል። የማትጠየቀው ፓስፖርት ብቻ ነው። አዲስ ሰው ከሆንክ “ከየት ነው የመጣኸው? ለምን ሥራ ነው የመጣኸው? እስኪ መታወቂያ” …. በቃ ምን አለፋችሁ የሀገራችን ክልል ሳይሆን ሌላ አዲስ ሀገር የምንገባ ነው የሚመስለው። ሰሞኑን በትግራይ ክልል ከአላማጣ መቀሌ፣አዲግራት፣አድዋ፣ አክሱም፣ሽሬ እንደስላሴን አልፌ ተከዘኔን አቋርጨ በሊማሊሞ አማራ ክልል እስግገባ በነበረኝ ቆይታ […]

የአማራው ፖለቲካ መጠለፍና ህወሓት በቀደደው ቦይ የመፍሰስ አደጋ! (መሀመድ አሊ መሀመድ)

01/01/2019 ከአማራው ፖለቲካዊ ትርክትና ሥነ-ልቦና አንፃር የዘር/የብሔር አደረጃጀትና አጀንዳዎቹ መገለጫዎቹና ቁመናውን የሚመጥኑ; ብሎም ዘላቂ ጥቅሙን የሚያረጋግጡ አይደሉም። አማራው በዚህ ጠባብ መንገድ ብዙ ርቀት ሊሄድና ሄዶም ብዙ ማትረፍ አይችልም። ይህን መንገድ ህወሓት ሄዶበታል። የህወሓት መንገድ መጨረሻው ገደል መሆኑን ቀድመው የተገነዘቡት ራሳቸው የድርጅቱ ጠንሳሾች ናቸው። አንዳንዶቹ ቀድመው ድርጅቱን ለቀዋል ወይም ተገፍተው እንዲወጡ ተደርገዋል። ድርጅቱ ያኔ በለጋ ዕድሜው […]

ገላሳ ዲልቦ፡ ከልጅ ሚካኤል እምሩ ዘመነ መንግሥት እስከ ዐብይ አሕመድ አገዛዝ ድረስ! (አቻምየለህ ታምሩ)

12/31/2018 ባለፈው ሳምንት አዲስ አበባ የገባው የኦነግ መሪ ገላሳ ዲልቦ ማተቡን ከመበጠሱ በፊት ወላጆቹ ያወጡለት ስም ዮሐንስ በንቲ ይባል ነበር። ዮሐንስ በንቲ በዘመነ ደርግ የልጅ ሚካኤል ካቢኔ ሳይፈርስ ደርግና በዙሪያው የተጠመጠሙ የግራ ድርጅቶች ያቋቋሙት ኅብረት የሆነው የሕዝብ ድርጅት ጊዜያዊ ፍሕፈት ቤት ባለሥልጣን የነበረ ሲሆን ለሁለት አመት ተኩል ያህል አለቃው የነበሩት አሰፋ ጫቦ ናቸው። አሰፋ ጫቦ […]

እኚህ አቶ ታዮ ደንድአ “የኦሮሞ ፎቢያ” አለባቸው እንዴ? (ያሬድ ሀይለ ማርያም)

12/31/2018 ኦነግ ገና እግሩ ሸገርን ከመርገጡ ለሕግ እና ለሥርዓት አልገዛም ሲል እና በአደባባይ ወጥቶ ትጥቄን አልፈታም፤ ማን አስፈቺ ማንስ ፈቺ ሊሆን ነው ሲል ነገሩ አላምር ስላለን ብዙ ሰዎች ድምጻችንን አሰምተናል። እኔም ‘ኦነግን እንደ ስለት ልጅ ማንቀራበጡ ይብቃ!’ በሚል የድርጅቱ ባህሪ በጊዜ በሕግ ካልተገራ አገሪቱን ወደ ከፋ ብጥብጥ ይሰዳታል በሚል አቤቱታ በማቅረቤ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የክልሉ […]