April 29, 2019
Source: https://mereja.com/amharic/v2/113101

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ምርጥ የጭነት አየር መንገድ በመባል ተሸለመ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እኤአ የ2019 የአፍሪካ ምርጥ የጭነት አየር መንገድ አገልግሎት ሽልማትን ተቀዳጀ።
ሽልማቱን ያዘጋጀው የኤር ካርጎ ኒውስ ተቋም በዓለም አቀፍ ደረጃ የካርጎ ዜናዎችን በመዘገብ፣ የኢንዱስትሪውን መሪዎች ቃለ መጠይቅ በማድረግና ኢንዱስትሪውን የተመለከቱ ትንታኔዎችን በመስራትና ለአለም አቀፍ የአየር ጭነት አገልግሎት ሰጪዎች ሪፖርቶችን በማዘጋጀት የታወቀ ነው።
በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው የአየር ጭነት አገልግሎት አቅራቢው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሽልማቱን ሚያዚያ 18 በእንግሊዝ ለንዴን ተቀብሏል።
“ቤስት ካርጎ ኤር ላይን 2019 “ተሸላሚ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዚህ በፊት ተደጋጋሚ ሽልማቶችን መቀዳጀቱንም ዘገባው አስታውሷል።
በኤር ካርጎ ኒውስ የሚዘጋጀው “የአመቱ ምርጥ የጭነት አየር መንገድ “ የሚሰኘው ሽልማት በዘርፉ የተከበረና ከፍተኛ እውቅና ያለው ሽልማት ነው።
ሽልማቱን አስመልክቶ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተወልደ ገብረ ማርያም”ይህነን የተከበረ ሽልማት በመቀዳጀታችን ከፍ ያለ ኩራት ተሰምቶናል ብለዋል።