በሰሜን ሸዋ ዞን ደብረ ብርሃን ሰላማዊ ሠልፍ ተካሄደ፡፡ ሰላማዊ ሠልፉ መፈናቀልና ግድያን በማውገዝ ነው እየተካሄደ ያለው:: ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃት እንዲቆምም ሠልፈኞቹ ጠይቀዋል::

የአማራ ወጣቶች ማኅበር በሸዋና የሸዋ ተወላጅ አማራዎች በጥምረት ያዘጋጁት ሠልፍ በደብረ ብርሃን እየተካሄደ ነው::
ሰላማዊ ሠልፉ መፈናቀልና ግድያን በማውገዝ ነው እየተካሄደ ያለው:: ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥቃት እንዲቆምም ሠልፈኞቹ ጠይቀዋል::
ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እንዲኖርና የደራ አማራ አስመላሽ ኮሚቴ አባላት እንዲፈቱም ጠይቀዋል:: በየቦታው ለሚፈጠር የአማራ መፈናቀልና ግድያ የፌደራል መንግሥት ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቀዋል:: እስካሁን የደረሰውንም ጥፋት አውግዘዋል::
የክልሉ መንግሥትም ለችግሮቹ መፍትሔ በአጭር ጊዜ እንዲያስቀምጥ ጠይቀዋል:: ሠላማዊ ሠልፉ አስፈላጊ መልዕክቶን አስተላልፎ በሠላም ተጠናቅቋል፡፡


