May 27, 2019

Source: https://fanabc.com

May 27, 2019 | by ethioexploreradmin | 0 Source: https://fanabc.com


አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19 ፣ 2011 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለቀጣዩ ሃገራዊ ምርጫ ማስኬጃ 3 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር እንዲፈቀድለት ለህዝብ ተወካዮች የበጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ።

ቦርዱ ተቋማዊ ለውጥ ካስተዋወቀበት ጊዜ ጀምሮ እየሰራቸው ባሉ ስራዎች ዙሪያ መግለጫ እየሰጠ ነው።

በመግለጫውም ለቀጣዩ ሃገራዊ ምርጫ 3 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር እንዲፈቀድለት መጠየቁን አስታውቋል።

የለውጥ ስራዎቹ ቦርዱን በህዝብ ተዓማኒ የሆነ ተቋም በማድረግ ለቀጣዩ ምርጫ ለማዘጋጀት ያለመ መሆኑም ተገልጿል።

ከዚህ ውስጥም ቦርዱ የህግ ማዕቀፎችን ማሻሻል፣ ተቋማዊ ማሻያዎችን ማድረግ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውይይት መድረክ ማዘጋጀትና ለፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ ማድረግ ይገኝበታል።

ከዚህ ባለፈም ከሲቪክ ማህበራት ጋር አብሮ መስራት የሚቻልበትን ሁኔታ ማሻሻልም ቦርዱ እያከናወናቸው ካሉ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።

በተጨማሪም ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በሚኖረው ትብብር ዙሪያ እየሰራቸው ያሉ ስራዎችንም በመግለጫው ጠቅሷል።