ጄነራል ሰዓረ እና ዶ/ር አምባቸው

ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ባህር ዳር ውስጥ የተከሰተው ነገር ለብዙዎች ያልተጠበቀ ነበር። ድንገት ከአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድሩ ቢሮ አካባቢ የተሰማው ተኩስ ለሰአታት ቀጥሎ ከተማዋን ያደናገጠ ሲሆን፤ ምን እንደተከሰተ ሳይታወቅ ቆይቶ የተኩስ ልውውጡ በሌሎች አካባቢዎችም አጋጥሟል።

የተኩሱ ምክንያት የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ መሆኑ በፌደራል መንግሥት ከተነገረ በኋላ እንደ ባህር ዳሩ ከባድ ባይሆንም አዲስ አበባ ውስጥ በጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዡ መኖሪያ ቤት አካባቢም ተኩስ ተሰምቶ ነበር።

ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን መገደላቸው ተነገረ

መፈንቅለ መንግሥቱና የግድያ ሙከራዎች

የሰኔ 16ቱ ጥቃትና ብዙም ያልተነገረላቸው ክስተቶች

በሁለቱ ከተሞች የተከሰተው ነገር በተቀራራቢ ጊዜ ያጋጠመ መሆኑ ደግሞ ምናልባት ተዛማጅ ጉዳዮች ሊሆኑ እንደሚችሉ ሲጠረጠር ነበር። ቅዳሜና ዕሁድ ምን ተከሰተ? ስለመፈንቅለ መንግሥት ሙከራውና ስለግድያው እስካሁን የምናውቃቸው ነገሮች ምንድን ናቸው?

ባህር ዳር

ቅዳሜ ሰኔ 16/2011 ዓ.ም

አዲስ አበባ

ቅዳሜ ሰኔ 16/2011 ዓ.ም

ዕሁድ ሰኔ 17/2011 ዓ.ም

የመከላከያ ሠራዊት በባህር ዳር ከተማ ከተሰማራ በኋላ ከመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው ፈጻሚዎች ውስጥ በቁጥጥር ስር የዋሉ እንዳሉና ያልተያዙ ሰዎች እንዳሉም እየተገለጸ ነው።

የአማራ ክልል ጊዜያዊ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ላቀ አያሌው ለክልሉ ቴሌቪዥን በሰጡት መግለጫ የጸጥታ ቢሮ ኃላፊ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ፅጌ እንዳልተያዙና እየተፈለጉ መሆናቸውን ተናግረዋል።

አዲስ አበባ ውስጥ በጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዡና ላይ በሌላ ጄነራል ላይ ጥቃት የፈጸመው ጠባቂ መያዙ የተገለጸ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሌሊት ላይ በሰጡት መግለጫ በድርጊቱ እጃቸው ያለበት በሙሉ ተጠያቂ እንደሚሆኑ አመልክተዋል።