August 19, 2019

አይፈተሹም የተባሉ የመከላከያ ሰራዊት መኪናዎች በሕዝብ ተቃውሞ እንዲቆሙ ተደርጓል።

Image may contain: one or more people, people riding bicycles, bicycle, motorcycle and outdoor

መተማ ላይ አምስት የመከላከያ መኪናዎች ወደ ሱዳን ለማለፍ ሲሞክሩ “አንፈተሽም” በማለታቸው ከሕዝቡ ጋር አለመግባባት ተፈጥሮ በሕዝብ ተቃውሞ እንዲቆሙ ከተደረገ በሆላ ተፈትሽው በመሳሪያ የሞሉ እንደነበር ተገለጸ።

የመከላከያ ሰራዊት አባላት “ወደ ዳርፉር እየሄድን ነው” ቢሉም ማለፊያም ሆነ ወደ ዳርፉር የሚሄዱበትን ማስረጃ ማቅረብ አለመቻላቸው ተገልጿል።

የመኪናዎቹ ታርጋዎች እንዳይለዩ በግሪስ የተቀቡ መሆናቸው በሕዝብ ጥርጣሬ መፍጠሩን የአካባቢው ምንጮች ገልፀዋል።

የመከላከያ ሰራዊት አባላት መኪናዎቹ እንዲፈተሹ ባለመፍቀዳቸው ሕዝቡ ኬላ ዘግቶ አስቁሞ ከክልሉ ልዩ ሃይሎች ጋር ባደረገው ፍተሻ ብዙ መሳሪያዎች ተገኝተዋል


እስካሁን ባለው ሁኔታ የዐማራ ክልል ልዩ_ኃይል እና ሕዝቡ ያቀረበው ጥያቄ ትክክል መሆኑን መግለፁ ተነግሯል።

Source -EthiopiaDJ