ኢሕአፓ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የሕብረተሰብ ክፍሎች አጋርነቱን እንደሚቀጥል አስታወቀ
የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) በኢትዮጵያ ውስጥ ለነፃነት፣ ለፍትሕ እና ለእኩልነት የሚያደርገውን ትግል እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡ ለአርሶ አደሮች፣ ለሠራተኞች ብሎም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኘው ማሕበረሰብ ሁሉ አጋር እንደሚሆንም ጠቁሟል፡፡
የፓርቲው የአመራር አባላት ካለፈው ነሐሴ 11 እና 12 ቀን 2011 ዓ.ም አዲስ አበባ ካዛንቺስ በሚገኘው የፓርቲው ጽሕፈት ቤት ጥናታዊ ጉባዔ አካሂደዋል፡፡ በጉባዔው ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የተውጣጡ አርባ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡ በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚኖሩ የወጣት ዘርፍ አመራሮችም በጉባዔው ተገኝተዋል፡፡
