September 4, 2019
Source: https://mereja.com/amharic/v2/143222
ባለፉት 28 ዓመታት ለደቡብ ክልል ከሲዳማ ውጭ የሌላ ብሄር ተወላጅ በርዕሰ-መስተዳደርነት ሲሾም አቶ ርስቱ ይርዳው ከአቶ ኃይለማርያም ቀጥሎ ሁለተኛ ሰው ሆነዋል።
ሌላ ምርጫ እስካልተካሄደ ክልሉን የሚመራው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ደኢህዴን/ በመሆኑ አዲስ ነገር አይፈጠርም ሲሉ የፖሊቲካ ሣይንስና የዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁር አቶ ዳያሞ ዳሌ ለቪኦኤ ተናግረዋል።
ክልሉን በምክትል ርዕሰ መስተዳደርነት ለመምራት በህዝብ እንደራሴዎች ፊት ቃለ-መሃላ የፈፀሙት አቶ ርስቱ ይርዳው በክልሉ አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥና የህግ የበላይነት ማስከበርን ቀዳሚ ተግባራቸው እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
አዲሱ የደቡብ ፕሬዚዳንት
by ቪኦኤ
