September 15, 2019

Source: https://mereja.com/amharic/v2/146302

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኃይማኖት ምዕመናን በቤተ ክርስቲያንና በምዕመኖቿ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ጣልቃ ገብነት ተቃወሙ

 
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ላይ የሚደርሱትን በደሎች በመቃወም ሰላማዊ ሰልፎች በመካሄድ ላይ ናቸው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ላይ የሚደርሱትን በደሎች በመቃወም በጎንደር፣ በደሴ፣ በደብረታቦር፣ በመቄት፣ በእስቴ፣ ወረታና በሌሎችም ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች ተደርገዋል። ሰልፈኞቹ በቤተ ክርስትያን ላይ የሚደርሰውን ቃጠሎ፣ በንብረት ላይ የሚደርሰውን ውድመት፣ በአማኞች ላይ የሚደርሰውን በደል በመቃወም ድምፃቸውን አሰምተዋል።
መንግስት ግዴታውን እንዲወጣ የጠየቁት ሰልፈኞቹ በቤተ ክርስትያንና በአማኞቹ ላይ በደል የሚያደርሱ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ አቅርበዋል።

Image
Image
Image
Image

በአዲስ አበባና በሌሎች ከተሞች ሰልፍ ይደረጋል ተብሎ የነበር ቢሆንም እንዲተላለፍ መደረጉ ይታወሳል።