November 23, 2019

Posted by: ዘ-ሐበሻ

ሲዳማ 10ኛው የኢትዮጵያ ክልል

የሲዳማ ዞን ቀጣይ ዕጣ ፈንታን ለመወሰን ረቡዕ ዕለት በተካሄደው ሕዝበ ውሳኔ ዞኑ የአገሪቱ 10ኛው ክልል የመሆን ድምጽ ማግኘቱን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ::

በዚህም መሰረት በሕዝበ ውሳኔው በመሳተፍ ድምጽ ከሰጠው ህዝብ ከሁለት ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት: ማለትም 98.51 በመቶው ዞኑ ክልል እንዲሆን የሚያስችለውን ድምጽ ሰጥተዋል::

በሕዝበ ውሳኔው ውጤት መሰረትም እስካሁን ድረስ ዞኑን በስሩ አድርጎ ሲያስተዳድረው የቆየው የደቡብ ክልል ኃላፊነቱን አዲስ ለሚመሰረተው የሲዳማ ክልል ያስተላልፋል::

ዋና መቀመጫውን በሲዳማ ዞን ውስጥ በምትገኘው በሐዋሳ ከተማ ያደረገው የደቡብ ክልል ለሁለት የምርጫ ዘመን ያህል መቀመጫውን ከአዲሱ የሲዳማ ክልል ጋር ተጋርቶ እንደሚቆይ ቀደም ሲል ተገልጿል::

በሕዝበ ውሳኔው መሰረት አዲስ የሚመሰረተው የሲዳማ ክልል ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቀጥታ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አንድ አባል ይሆናል::

#etv የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ድምጽ ውጤት

#etv የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ድምጽ ውጤት

Posted by Ethiopian Broadcasting Corporation on Saturday, November 23, 2019