November 29, 2019

Source: https://mereja.com/amharic/v2/177059

– ኳታር የተለያዩ የሽብርና የተቃውሞ ተግባራት በኤርትራ ውስጥ እንዲፈጸሙ የማስተባበር ሥራዎችን እያከናወነች መሆኑን እንደደረሰበት የኤርትራ መንግሥት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
– የኤርትራ መንግሥት የማስታወቂያ ሚኒስቴር “ከክስና ሐሰተኛ መረጃዎችን ከመጠቀም ይልቅ እውነታዎችንና የችግሮቹን ስር መሰረት መለስ ብሎ እንዲመረምር” የኳታር የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቅርቧል።
BBC Amharic : ኳታር የተለያዩ ኃይሎችን በመጠቀም የአገሪቱን ከፍተኛ ባለስልጣናት ለመግደል ዕቅድ እንዳላት እንደደረሰበት የኤርትራ መንግሥት ይፋ አደረገ።
የኤርትራ መንግሥት ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳለው ኳታር የተለያዩ የሽብርና የተቃውሞ ተግባራት በኤርትራ ውስጥ እንዲፈጸሙ የማስተባበር ሥራዎችን እያከናወነች መሆኑን እንደደረሰበትም አስታወቀ።
ለዚህም ተግባር ጎረቤት ሱዳንን እንደ ድልድይ በመጠቀም የአገሪቱን ሰላም ለማደፍረስ የተለያዩ ተግባራት በኳታር ደጋፊነት እየተከናወኑ መሆናቸውን የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ላይ አመልክቷል።
ኳታር ከፍተኛ ባለስልጣኖቼን ለመግደል ዕቅድ አላት በማለት ኤርትራ ያቀረበቸውን ክስ የኳታር መንግሥት አጣጣለው።
በኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስቴር በኩል ለወጣው ክስ አዘል መግለጫ ኳታር በሰጠችው ምላሽ “ሐሰት” በማለት ክሱን ሙሉ ለሙሉ ውድቅ አድርጋዋለች።
የኤርትራ መንግሥት በተጨማሪም ኳታር ተቃዋሚ ቡድኖችን በመደገፍ በኤርትራ መንግሥት ላይ አመጽና ተቃውሞን ለመቀስቀስ መጣሯን በክሱ ላይ አመልክቷል።
ኳታር ባወጣችው መግለጫ የኤርትራ መንግሥት ከጠቀሳቸው የትኛውም አንጃ ሆነ ቡድን ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌላት በመግለጽ “ይህንንም የኤርትራ መንግሥት በደንብ ያውቀዋል” ብላለች።
‘ኳታርና ተላላኪዎቿ’ እብደታቸው እያደገ ነው ብሎ የሚጀምረው መግለጫው “ኳታርና ሸሪኮቿ የኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚዎችና የፖለቲካ መሪዎች እንዲሁም ወጣቶችን በመቀስቀስ የጦር መሳሪያ እንዲታጠቁና ተቃውሞ እንዲያስነሱ ተዘጋጅታለች” ሲል ይከሳል።
መግለጫው