2019-12-21

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በወቅታዊ ሁኔታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መግለጫ

. በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በደረሰው ወቅታዊ እና ያልታሰበ ጉዳት በሐዘን ላይ የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናንና ምዕመናት: የኢትዮጵያ እስልምና  ጠቅላይ ምክር ቤት እና የመጅሊስ  አባላት የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ወገኖቻችን፦ • በአማራ ክልል በምሥራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ወረዳ  በቤተ እምነቶች  ላይ የቃጠሎ ጉዳት መድረሱን ከተለያዩ  የመረጃ ምንጮች  ሰምተናል። በጉዳቱም  የተሰማንን ልባዊ ሐዘን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንገልጻለን። • የተፈጸመው ድርጊት የሀገራችን ሰላም እና እድገት የማይጠቅም ለዘመናት የቆየ አብሮነት የመኖር ዕሴቶቻችን የሚንድ  መሆኑን መላው ሕዝባችን  ተረድቶ  በተረጋጋ እና በሰከነ መንፈስ ጉዳዩ እስከሚጣራ  በትእግስት እንድትጠባበቁ እናሳስባለን። • ከዚሁም  ጋር  የሚመለከታችሁ የመንግሥት አካላት ለጉዳዩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት  አስፈላጊው ክትትል እንድታደርጉ  እናሳስባለን። • ይኽንኑ ድርጊት አስመልክቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሚመለከተው የመንግሥት  የአስተዳደር :የሕግ እና የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን አጣርተን ይፋ የምናደርግ መሆኑን በአጽንዖት እንገልጻለን። • እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!! መ/ር ኃይሉ በላይ EOTC TV Filed in:Amharic