January 7, 2020

Source: https://www.zehabesha.com/amharic/archives/100193

በግሎባል ፋየር ፓወርስ ጥናት መሠረት፣ በአፍሪካ አህጉር ከፍተኛ ወታደራዊ ተቆም የገነቡ አምስት አገራቶች ውስጥ በአንደኛ ደረጃ ግብፅ ስትሆን፣ሁለተኛ አልጀሪያ፣ ሦስተኛ ሳውዝ አፍሪካ፣ አራተኛ ናይጀሪያ እንዲሁም አምስተኛ ደረጃ ኢትዮጵያ መሆናቸውን ግሎባል ፋየር ፓወርስ (Global Firepower’s 2019 Military Strength ranking) በ2019 እኤአ ወታደራዊ ጥንካሬና ደረጃ እንዳላቸው ገልፆል፡፡

ግሎባል ፋየር ፓወርስ ጥናት 50 ወታደራዊ መለኪያዎችና የብሔራዊ ኃይል መሥፈርቶች (Nation’s Power Index Score) ውስጥ ትኩረት ያደረገው በየአገሮቹ ያለ የመሳሪያ ክምችት ዓይነት፣ ጥራትና ዘመናዊነት፣ የሠለጠነ ወታደራዊ የሰው ኃይል፣ የሥነ መልክአ ምድር ስትራቴጂክ አቀማመጥ፣ ወታደራዊ ስንቅና ትጥቅ አቅርቦት እንዲሁም የተፈጥሮ ኃብት ወሳኝ መለኪያዎች ናቸው፡፡ አምስቱ የአፍሪካ ሃገራት ከፍተኛ ወታደራዊ  ተቆም የገነቡ ሃራት ሲሆኑ በውትድርናው መስክ ሃገር በቀል ወታደራዊ መከላከያ ኢንዱስትሪ  በመገንባት መሪነቱን ለመጨበጥ ችለዋል፡፡ ወታደራዊ መለኪያዎችና መሥፈርቶች ውስጥ ዋናዎቹ ተዋጊ የጦር አውሮፕላን፣ ተዋጊ ታንኮች፣ የባህር ኃይል፣ የመከላከያ ባጀት አንኮሮቹ ናቸው፡፡

በ2018 እኤአ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የሦስተኛ ደረጃ የነበራት ሲሆን በ2019 እኤአ ወደ አምስተኛ ደረጃ ዝቅ ብላለች፡፡ በተመሳሳይ አመተምህረት ደቡብ አፍሪካ ከአምስተኛ ደረጃ ወደ ሦስተኛ ደረጃ ከፍ ብላለች፡፡

ግሎባል ፋየር ፓወርስ ጥናት መሠረት፣ ወታደራዊ የኃይል አመዳደብ ደረጃ (Power Index Score is 0.0000) ሊደረስበት የማይችል መለኪያ ሲሆን ወደዚህ አሃዝ በደረሱና በተጠጉ ቁጥር የአገሮች መከላከያ ኃይል ጥንካሬን ያረጋግጣል፡፡

አምስቱ ኃያላን የአፍሪካ አህጉር ወታደራዊ ኃይል ተቆማት በ2019እኤአ

These are the 5 most powerful militaries in Africa in 2019

የውጭ አንበሣ የውስጥ እሬሳ!!! የህወሓትና ኦነግ ሽብርተኝነትና የፖለቲካ ሴራ

ምንጭ፡-