January 11, 2020
Source: https://mereja.com/amharic/v2/198127
https://radiodownloaddw-a.akamaihd.net/Events/dwelle/dira/mp3/amh/318511A2_2_dwdownload.mp3
DW : የአዲስ አበባ ባለ አደራ ምክር ቤት ወደ ፖለቲካ ፓርቲነት በይፋ መለወጡን የምክር ቤቱ ሰብሳቢ እስክንድር ነጋ አስታወቁ።አቶ እስክንድር ነጋ እንዳስታወቁት አምና መጋቢት የተመሠረተዉ ምክር ቤት የፊታችን ሰኞ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓርቲነት እዉቅ እንዲሰጠዉ ይጠይቃል። አቶ እስክንድር ለጋዜጠኞች እንደነገሩት ፓርቲያቸዉ በሚቀጥለዉ ምርጫ አዲስ አበባ ዉስጥ የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ያቀርባል፤ ከሌሎች ሐገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር «ሐገራዊ አማራጭ» የሚሆን ጥምረት ወይም ቅንጅት ይመሰርታልም።