የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የዘንድሮው ምርጫ የድምፅ መስጫ ቀን ነሃሴ 10/2012 እንዲሆን ሃሳብ አቅርቧል።

ቦርዱ የድምፅ መስጫ ቀንና ሌሎች ከምርጫ ጋር የተገናኙ ክስተቶች የሚከወኑበትን የጊዜ ሰሌዳ ለውይይት ክፍት አድርጓል።

ቦርዱ፤ የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት አስተያየትና ግብዓት እየሰጡበት የሚገኝ ሲሆን፤ በውይይቱ እየተሳተፉ የሚገኙት ባለድርሻ አካላት ምርጫው በነሃሴ ወር እንዲካሄድ መታቀዱ ትክክል አይደለም ብለዋል።

ከታኅሣሥ 22 ጀምሮ እስከ መጋቢት መባቻ ድረስ የክልል ምርጫ ቢሮዎች የሚደራጁበት ነው ተብሏል።

ከመጋቢት 29 እስከ ሚያዚያ 28 ያለው የአንድ ወር ጊዜ ለመራጮች ምዝገባ ሊውል እንዲሚችል ቦርዱ ያወጣው ፍኖተ ካርታ ያሳያል። ከሚያዚያ አጋማሽ እስከ 26 ባለው ጊዜ ደግሞ ዕጩዎች ይመዘገባሉ።

የፖለቲካ ፓርቲዎች በይፋ የምረጡን ዘመቻቸውን የሚጀምሩት ሚያዚያ 27 ሲሆን፤ ነሃሴ 05 ደግሞ የማብቂያ ጊዜ እንዲሆን ሃሳብ ቀርቧል።

End of Facebook post by National Electoral Board of Ethiopia- NEBE –የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Skip Facebook post by National Electoral Board of Ethiopia- NEBE –የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የምርጫው ቅድመ ውጤት ከድምፅ መስጫው ቀን ማግስት ነሃሴ 11-15 ባለው ጊዜ ይፋ እንደሚሆን የቦርዱ ረቂቅ ሰሌዳ ያሳያል። እስከ ነሃሴ ባለው ጊዜ የቦርዱ የተረጋገጠበት ውጤት ማሳወቂያ ጊዜ ነው ተብሏል።

ቦርዱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ላይ ተወያይቶ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል።