April 13, 2020 |

ሚያዚያ 13, 2020

Source: https://amharic.voanews.com/a/wolqait-committee-arrest-4-13-2020/5370444.html
https://gdb.voanews.com/A0B34EB6-FDEB-47C1-A3EF-9BEC2160F931_cx0_cy8_cw0_w800_h450.jpg

የኢትዮጵያ ካርታ

የኢትዮጵያ ካርታ

ባህር ዳር —  የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰሞኑን አባሎቻችን ያለ ምንም ምክንያት ታሰረውብናል ሲል ቅሬታ አቀረበ።

የወልቃይት አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታላይ ዛፌ አቶ መብራቱ ጌታሁንን ጨምሮ ወደ 4 የሚጠጉ አባሎቻችን ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ጎንደር ከተማ ውስጥ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው ታስረውብናል ብለዋል።
በእስር ላይ የሚገኙት የአቶ መብራቱ ልጅ ደግሞ አባቴ የታሰረው ፋኖ ነህ ተብሎ ነው ትላለች
በጉዳዮ ዙሪያ የመንግሥትን አካል ለማናገር የተደረገው ጥረት አልተሳካም።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ አባላት እስር

by ቪኦኤ