April 23, 2020
Posted by: ዘ-ሐበሻ

የሻብያው አንባገነን መሪ ኢሳያስ አፈወርቂና የኤርትራ የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ጂ 15 በወህኒ ቤት 20 አመታት ሞላቸው!!!
‹‹በምን አወቅሽበት በመመላለሱ
ሲታሰር ወደ እኔ፣ ሲፈታ ወደ እሱ!!!››
የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግሥት መርህ አልባ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የመከላከያ ኃይል ግንኙነት በጊዜው መልክ ሊይዝ ይገባል እንላለን፡፡ የሻቢያ፣ ወያኔና ኦነግ የጦር አበጋዞች መርህ አልባ የፖለቲካ ግንኙነትና የመቶ ዓመት ስውር የፖለቲካ ሴራ ቀጣይ ፍንጮች ይስተዋላሉ፡፡
- በአንድ በኩል በቅኝ ገዥነት የፈረጁትና የኢትዮጵያን አንድነትና፣ ብሄራዊ ፍቅር ያስጠብቃል የሚሉትን የአማራ ህዝብ መምታትና ማስመታት የሻቢያ፣ ወያኔና ኦነግ የጦር አበጋዞች የቆየ የጋራ የፖለቲካ አቆም ነው፡፡
- በሌላ በኩል በሃገራችን ፋሽን የሆነውን በብሄርተኛነት መደራጀት መብት የተነፈገው የአማራ ብሄርተኛነት ተጠናክሮ ከቀጠለና የአማራ መደራጀትና መታጠቅ የሚያስፈራቸው የሻቢያ፣ ወያኔና ኦነግ የጦር አበጋዞች በአማራ ክልል የአስቸኮኳይ ጊዜ አዋጅ፣ ኮማንድ ፖስቱ ታንኮችና ከባድ መሣሪያ ይዞ መግባት ለኮሮናቫይረስ በሽታ ማስወገድ ነው ቢባልም ለአማራ ህዝብ የሚታገሉ መኢአድ፣ አብን፣ ፋኖ፣ ከግንቦት 7 ታጋይ አርበኞችና ምሁራንን ለማጥቃት በማሴር ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡ ወያኔ በትረ ሥልጣኑን ለኦህዴድ/ ኦዴድ ብልፅግና በማስረከብ በጋራ ባላቸው አቆም የአማራ ክልል ለማጥቃት የዘመተው መከላከያ ሠራዊት በአንድ በኩል በትግራይ በኩልና በሌላ በኩል በወለጋ በኩል አድርጎ መግባቱ አሁንም የአማራን ህዝብ ለመበቀል የጋራ የፀና አቆም እንዳላቸው ያመላክታል፡፡ ወያኔ ከአማራ ክልልና ከአፋር ክልል በጉልበት የነጠቀውን መሬት ይዞ ለመቀጠል የአማራ ህዝብ ደካማ መሆን ስላለበት የዶክተር አብይን ዘመቻ ወያኔም ይፈልገዋል፣ የአማራን ዘርፈ ብዙ ጥቃት ወያኔ ያስተባብራል ብሎም ያቀናጃል፡፡
- ኢዜማ በዜግነት ፓርቲ፣ በህብረ-ብሄር ፓርቲ ስም እየታገልኩ ነው እያለ በአማራ ክልል ተወዳድሮ ለማሸነፍ ቆምጦል፣ የአማራ ህዝብ ከእኛ ዘንድ አትድረስ፣ ‹‹ አማራ የሚባል ብሄር የለም፣ አማርኛ መግባቢያ ቆንቆ እንጂ ዘር አይደለም!!›› ብላችኃል ይላሉ ፕሮፊሰር ብርሃኑ ነጋና አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የፖለቲካው ሴራ ሚስጢሩ መኢአድ፣ አብን፣ ፋኖን፣ ባልደራስ መኢአድ ወዘተ ትጥቅ ለማስፈታትና ለማስገበር ነው፡፡ ኦነግ/ኦዴፓ ብልፅግና ኢዜማ በዚህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፣በ5ወራት ውስጥ የሚሰሩት ተቃዎሚ ፓርቲዎችንና ጋዜጠኞችን በመክሰስና በማሰር ያሳልፉታል፡፡
- የኦሮሞ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦነግ) ኦህዴድ/ ኦዴድ ብልፅግና የአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተሞች የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ስር መካለል እንዳለበት ሻብያና ወያኔ ኦህዴድ/ ኦዴፓ/ ብልጽግና ኢዜማ ገፀ በረከት ማቅረባቸው ቀጣይ የፖለቲካ ሴራ ነው ንቃ እንላለን፡፡ የንጉስ ሚንልክና የእቴጌ ጣይቱ የቆረቆሮት አዲስ አበባ ከተማ፣ የአፄ ሚኒልክ ቤተመንግስት የተገነባበት፣ የእቴጌ ጣይቱ ሆቴል፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ መንግስታዊ ተቆማቶች፣ መስሪያ ቤቶች ፣ ቤተክርስቲያን፣ መስጊድ፣ የእምነት ቦታዎች የተገነቡበት፣ የአፍሪካ ህብረት፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ቦሌ አየር ማረፍያ፣ ኢንባሲዎችና ለጋሲኖች ወዘተ የተገነቡበትን የአንድ ብሄር ነው ማለት ገንቢዎቹም ትግስት እንጅ የሚቀሰቀሰው የማያባራ ጦርነት ሃገር ይጎዳል እንላለን፡፡
- ሻብያ ኦነግ ትጥቁን ሳይፈታ በትግራይ በወያኔ በኩል በአቦይ ስብሃት ተባርኮ የገባውን ማስታወስ ብልህነት ነው እንላለን፡፡ የሻቢያ፣ ወያኔና ኦነግ የጦር አበጋዞች ኢትዮጵያ የምትባለውን ሃገር ከአስር ትንንሽ ወደ መቶ ትንንሽ ክልላዊ መንግስትነት በመከፋፈል በወሰንና ድንበር የማያባራ ጦርነትና ግጭት ከትቶ የእራሳቸውን ህልውና የማስጠበቅ የመቶ ዓመት ስውር የፖለቲካ ሴራን በመተግበር ላይ ይገኛሉ፡፡ ዘረኛ የጦር አበጋዞች ክልላዊ መንግስቶች እንደ አሸን በፈሉ ቁጥር የድንበርና የወሰን የጦርነት ግጭቶች እንደ ሰደድ እሳት ይዛመታል ጦሱም እንደ ሶሪያ፣ የመን፣ ሊቢያ ፣ አፍጋኒስታ፣ ኢራቅ ህዝብ የጦር አውድማ፣ የማያባራ የውክልና ጦርነት መዛመቱን ማስታዋል ይገባል እንላለን፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ተሰደው የመጡትን የሱማሌ፣የሶሪያና የየመን ዜጎችን እያየን ከእነሱ መማር የጊዜው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው እንላለን፡፡ ሃገራችን ለሁላችንም ትበቃለች ፍቅር ይስጠን እንላለን፡፡
የሻቢያ፣ ወያኔና ኦነግ የጦር አበጋዞች በኤርትራም፣ በትግራይና፣ በኦሮሞ ስም አስሬ ቢምሉም ቢገዘቱም፣ የህዝቡ እጣ ፈንታ ሞት፣ እስራትና ስደት በቀር የተረፈው ነገር የለም፡፡ የጦር አበጋዞቹና በስልጣን ሱስ በሰከሩ፣ አድርባይ ምሁራን በዴሞክራሲ ስም፣ በፌዴሮሽን ስም፣ በህገ-መንግሥት ስም በህዝብ ላይ ጥቃት ይፈፅማሉ፡፡ የሻቢያ፣ ወያኔና ኦነግ የጦር አበጋዞች ከህዝብ በዘረፉት ኃብትና ንብረት ተንደላቀው ይኖራሉ፡፡ ወያኔ ዘርፎ ትግራይ ገብቶል፣ ኦነግም ዘርፎ ወለጋ መሽጎል፣ ኦህዴድ/ ኦዴፓ ብልጽግናም የመቶውን አመት ስውር የፖለቲካ ሴራ ለማስፈፀም ላይ ታች ይላል፡፡ የፖለቲካው ሴራ ሲተነተን እንኮን ለኢትዮጵያ ህዝብ ለክልላቸውም ህዝብ እንደማይበጁ እውነተኛ ማስረጃውን እንሆ እንላለን፡-
ህዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ (ህግሓት) ከኢትዮጵያ ቅኝ ግዛትነት ለመውጥት ሲታገል ቆይቶ በሜይ 24 ቀን 1993 እኤአ ነፃ ወጥቻለሁ ይላል፡፡ ሻቢያ አንድ አውራ ፓርቲና ብቸኛ መንግሥት በመሆን ላለፉት 27 አመታት ሕገ መንግስትና ዴሞክራሲና ምርጫ ገለመሌ የሚባል ዜና ፖለቲካና ሃተታ ሳይኖር በአንባገነንነት የገዛ የማፍያ ድርጅት ነው፡፡ የህግሓት መንግስት የስብዓዊ መብት ምህደር በዓለማችን ካሉት ነፃነት ደፍጣጮች የመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ የኤርትራ መንግሥት የመገናኛ ብዙሃንና ፕሬስ ነፃነት በዓለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት ማህደር በመጨረሻነት ከሰሜን ኮሪያን አፋኝነት ተርታ ተሰልፋለች፡፡ የኤርትራ መንግስት መርህ አልባ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶች በማድረግ ከአፍሪካ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ኢጋድ እንዲሁም በአረብ ሊግ በታዛቢነት አባል መሆን ችሎል፡፡ ኤርትራ 117,600 ኪሎሜትር ስኩየር የቆዳ ስፋት ሲኖራት የቀይ ባህር የባህር በር አላት፡፡ ኤርትራ ህብረ ብሄር ሀገር ስትሆን የህዝብ የቌንቌ ስብጥር ዘጠኝ ዘውጌ ቡድኖች ይገኛሉ ከነዚህ ውስጥ፣ ትግርኛ 55 በመቶ፣ ትግረ 30 በመቶ፣ ሳሆ 4 በመቶ፣ ኩናማ 2 በመቶ፣ ቢለን 2 በመቶ፣ ራሻይዳ 2 በመቶ እንዲሁም የተለያዩ 5 በመቶ ዘውጌ ብሄር ብሄረሰቦች ቢኖሩም በዘር መደራጀትና እራስን በራስ እስከመገንጠል መብት የሚባል ገለመሌ የለም፡፡ በ2016 እኤአ የሥነ-ህዝብ ብዛት ቆጠራ 4,954,645 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሃገር ናት፡፡
ኢሳያስ አፈወርቂ ተቃዋሚ ፖለቲካ የነበሩትን ጂ 15 በመባል የሚታወቁትን የህሊና እስረኞች በአሰቃቂ ሁኔታ በማሰር በአለም ህብረተሰብ በአንባገነን ገዢነታቸው የሚታወቁ ሲሆን ዶክተር ብርሃኑ ነጋ፣ አንዳርጋቸው ፅጌ የፖለቲካ ሴራ ጠንሳሽነትና ኦቦ አብይ አህመድ፣ አሽቃባጭነት ሊወድቅ ተንገዳግዶ የነበረው የኢሳያስ ፋሽስታዊ አገዛዝ እንደ እባብ አፈር ልሶ ዳግም ተነሳ፡፡
የጂ 15 የፖለቲካ እስረኞች The “G-15” Prisoners የኤርትራ አስራአንድ ከፍተኛ ሹማምንቶችና አስር ነፃ ጋዜጠኞች ከታሰሩ 20 አመታት አለፋቸው፡፡
These are the 11 government/party critics who were arrested and are believed to have been held in solitary confinement since September 2001. Five of them (designated by asterisks) are presumed dead based on credible reports discussed later in this report:1
- መሃሙድ አህመድ ሸሪፎ (በህይወት የሌለ) *Mahmoud Ahmed Sherifo (born 1947), former foreign minister and former minister of local government; also former chairman of the committee drafting Eritrea’s proposed electoral law;
- ሃይሌ ወልደትንሳይ Haile Woldetensae (born 1947), former foreign minister and former minister of trade and industry;
- ጴጥሮስ ሰሎሞን Petros Solomon (born 1948), former minister of defense; former minister of maritime resources; former Eritrean People’s Liberation Front (EPLF) chief of intelligence;[1]
- በራካይ ገብረስላሴ Berakai Ghebreselassie (born 1946), former minister of information; former minister of education; ambassador to Germany;
- ብ/ጀ እስጢፋኖስ ስዩም Brigadier General Estifanos Seyoum (born 1947), former director-general of inland-revenue;
- ሜ/ጀ ብርሃኔ ገረግዜር Major General Berhane Gerezgiher (born 1947), former commander of the armed forces; former head of the national reserve force;
- ሜ/ጀ እቁባይ አብርሃ (በህይወት የሌለ) *Major General Ogbe Abraha (born 1948), former chief of staff of the armed forces; former minister of trade and industry; former minister of labor and social welfare;
- ሳለህ ኢድሪስ ከክያ Saleh Idris Kekya (born 1950), former minister of transport and communication; former director of the president’s office;
- አስቴር ፍስሃፂዮን (በህይወት የሌለ) *Aster Fezhazion (or Fesshatsion) (born 1951), Mahmoud Sherifo’s wife, the only woman arrested on September 18-19, former regional head of personnel;
- ሃሚድ ሂሚድሃመድ (በህይወት የሌለ) *Hamed Himid Hamad (born 1955), former director of Arabic section of the ministry of foreign affairs; former member of the People’s Front for Democracy and Justice executive council;
- ግርማኖ ናቲ (በህይወት የሌለ) *Germano Nati (born 1946), former regional director of social affairs.
“The 20 men and one woman arrested in September 2001—11 high government officials and 10 independent journalists—have never been seen again. They have collectively come to be known as the G-15 because the original group of signatories to a manifesto critical of the government numbered 15. The government has provided no information about their whereabouts or conditions in the decade since their arrests. What is known about them has been garnered largely from information supplied by defectors who have fled the country. Kept hidden in a secret detention facility, 10 of the 21 have died in prison according to reports that Human Rights Watch has not been able to independently confirm. The others remain in solitary confinement, physically or mentally incapacitated, and emaciated. None of the 21 has been formally charged with a crime, much less convicted. Since the arrest of the journalists and closure of their newspapers, no independent news media have been allowed in Eritrea.”2
የኤርትራም ህዝባዊ ትግል በሻቢያ መርህ አልባ የአፍሪካ ቀንድ የበላይ የመሆን የፖለቲካ ሴራ የተነሳ ከጎረቤት አገራቶች ጋር ሁሉ ጠብያለሽ በዳቦ ሆነ፡፡ ሻብያ ከየመን በሃኒሽ ደሴት፣ ከጅቡቲ፣ ከኢትዮጵያ፣ ከሱዳን ወዘተ ጋር አንባጎሮ ገጠመ፣ በዚህም የተነሳ ከዓለም አቀፍ ማህበራት ጋር የዲፕሎማሲ ግንኙነቶቹ ተበጣጠሱ፡፡ የሻብያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ የአፍሪካ ሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጁንግ ኡንንነት ተፈረጁ፡፡ በመለስ ዜናዊ ዘመን ኤርትራ በአሜሪካና የተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚና የጦር መሳሪያ ግዝ ማዕቀብ ተጣለባት፡፡ ኢትዮጵያና ኤርትራ ከጦርነቱ በኃላ ኢኮኖሚያው ቀነጨረ፣ የመከላከያ ሠራዊታቸው አከርካሪው ተመታ፣ የስብዓዊ መብትና ጥሰትና የዴሞክራሲ አፈና ተስፋፋ፣ ሞት፣ እስራትና ግርፈት መጨቆኛ መሳሪያቸው ሆነ፡፡ ህዝባቸውም ተስፋ በመቁረጥ ወደ ጎረቤት ሃገሮች ላለፈው ሁለት አስርታት ተሰደደ፡፡ የወጣቱ መፈክር ‹‹ለመኖር ሂድ/ተሰደድ!!›› ሲሆን በአንፃሩ የድንበር ጠባቂው ወታደር ‹‹ተኩስ ለመግደል!!›› ይላል፡፡ በ2011 እአኤአ 222,000 የኤርትራ ስደተኞች ከህዝቡ ቁጥር 5 በመቶ የተሰደደ ሲሆን በየወሩ 3000 ሽህ ወጣቶች ድንበር አቆርጠው ይሰደዳሉ፡፡ ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራን ከኢትዮጵያ ገንጥሎ ለህዝቡ ያበረከተው ገፀ በረከት ይሄ ሲሆን ከዚህ የማይማሩ የእኛ ዘረኛ የጦር አበጋዞች ህወሓት ትግራይን ገንጥሎ ህዝቡን በምድር ሲኦል እንደሚከቱት ይታወቃል፣ ኦነግ ኦሮሚያን ገንጥሎ ህዝቡን በምድር ሲኦል እንደሚከቱት ይታወቃል፡፡ “Despite the mortal danger of trying to escape the country, Eritrea’s most significant export over the past decade has been its fleeing citizens. Eritrea’s youths have adopted a secret motto: “Leave to live!” Despite border guards’ shoot-to-kill orders, the exodus persists. Over 222,000 Eritreans (almost five percent of the population) had fled the country as of January 2011, with about 3,000 fleeing per month.”
የኢትዮጵያና የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይሎች አንድም ቀን ከኢትዮጵያ ወይም ኤርትራ ህዝባዊ ትግል ጎን ቆሞው መለስ ዜናዊን ወይም ኢሳያስ አፈወርቂን ሲቃወሙ ተሰምተው አይታወቅም፡፡ የኢሳያስን ፋሽስታዊ አገዛዝ ዲሞክራቶቹ ብርሃኑ ነጋና አንዳርጋቸው ጽጌ እያወደሱ ወያኔን ‹‹ነጻነትን የማያውቁ ነፃ አውጭዎች›› እያሉ ሻብያን ያለማለት ማፍያዊ መርህ አልባ አቆም ነው እንላለን፡፡ የኤርትራ የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ጂ15ቶች ላይ የሚደርሰው የስብዓዊ መብቶች ጥሰት፣ የዴሞክራሲያዊ መብቶች አፈና፣ የግፍ እስራት ዓለም ሲያወግዘው እናንተ የኢሳያስ ቡችሎች ግንቦት ሰባት፣ ኦነግ፣ ደህሚት፣ ወዘተዎች አሳፋሪ አቆም በታሪክ ያስጠይቃል፡፡ ኤርትራ በርሃ እያላችሁ ‹‹ ባትዋጋ እንኮን በል እንገፍ እንገፍ፣ የአባትህ ጋሻ ትሆኑ ይርገፍ!!!›› ተብሎ ተዘፍኖላችሁ ነበር፡፡ ለኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ቀን ሳትደርሱለት፣ እንደ ሳይላክ የቀረው ደብዳቤ ‹‹ሳይዘምት የተመለሰው ነፃ አውጭ›› ብሎ ግንቦት 7 ይጻፍላችሁ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያና የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይሎች የጋራ ህብረት ፈጥረው ለነጻነት፣ ለዴሞክራሲና እኩልነት ቢታገሉ ኖሮ የሻብያና የወያኔ አንባገነን መሪዎች አገዛዝ በአጭር ይቀጭ ነበር እንላለን፡፡
- ኢትዮጵያና ኤርትራ በድንበሮች ባድማ፣ ፆረና፣ ኢሮፕ ወስን ግጭት የተነሳ የኢትዮጵያ ህወሓት መለስ ዜናዊና የህግሓት ኢሳያስ አፈወርቂ ከ1998 እስከ 2000 እኤአ ጦርነት ገጠሙ፣ ከ70 እስከ 100 ሽህ ወታደሮች በጦርነቱ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ በሃገራቱ የኢኮኖሚ ዘርፎችም በብዙ ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሃብትና ንብረት በጦርነቱ ወድሞል፡፡ ዶክተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያና ኤርትራ ይግባኝ የሌለው ፍርድ የሄጉን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያደርጉት ጥረት ሁሉን አሳታፊና ግልፅ መሆን ይኖርበታል፡፡
- የኢትዮጵያና የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በመርህ ላይ የተመሠረተ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ተፎካካሪ ፓርቲዎች መክረውበት፣ ምሁራን አጥንተውት በፓርላማ መጽደቅ ይኖርበታል እንላለን፡፡ ዶክተር አብይ አህመድ ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ያደረጉት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ ጉዳይና የመከላከያ ግንኙነቶች በመርህ ላይ የተመሠረተ ግንኙነት ለህዝብ ይፋ መሆን አለባቸው እንላለን፡፡ በሁለቱ ሃገራት መኃል ያለውም የድንበር ግጭት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በአግባቡ መፈታት ይኖርበታል እንላለን፡፡
- የኤርትራ ህዝብ በተለይም ወጣቶች ብሄራዊ የውትድርና አገልግሎት ስልጠና እንዲወስዱ በማስገደድ ወጣቶች ጊዜቸውን ከትምህርት ይልቅ የጦርነት አባዜ አውዳሚ ኢኮኖሚ ያስከተለው ወጣቶችን ለሞት፣ እስራትና ስደት ተዳርገዋል፡፡ የኤርትራ ወጣቶች በገዛ ሃገራቸው መኖር ተስኖቸው ድንበር አቆርጠው፣ በርሃ አቆርጠው፣ ውቅያኖስ ሰንጥቀው፣ በህይወትና ሞት ትግል ያለቀው አልቆ በህይወት የተረፉት በስደት ለመኖር ተገደዋል፡፡ ለዚህም ተጠያቂው የእድሜ ልክ ፕሬዜዳንቱ የሻቢያው ኢሳያስ አፈወርቂ ለነፃነት፣ ለዴሞክራሲና እኩልነት የታገሉበት የትግል ውጤቱ ባርነት፣ ሞት፣ እስራትና ስደት መሆኑን የኤርትራ ህዝብ ምስክር ነው፡፡ ይሄንን ፋሽስት መሪ ነው ‹‹ኢሱ!!!…ኢሱ!!!›› እያለ የሚያቆላምፀው ኦቦ አብይ አህመድ ‹‹ስኮርት!›› አንባገነኑ ኢሳያስ አፈወርቂ በገነባው 300 እስር ቤቶች፣ የመሬት በታች የጉድጎድ ወህኒ ቤቶች፣ የኮንቴይነር እስር ቤቶች ውስጥ ዜጎቹን በማጎር እስረኞቹ ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶች በመፈፀም ምግብ ፣ ውኃና የህክምና አገልግሎት በመንፈግ የፖለቲካ ተቃዋሚዎቹንና የኃይማኖት እምነት ተከታዬችን በማሰቃየት ይታወቃል፡፡ ”Since 2002 the 18-month national service requirement for Eritreans over the age of 18 has been extended indefinitely. …. Thousands of political prisoners and others who violated the terms of their national service by deserting or attempting to desert languish indefinitely in overcrowded detention centers, including underground cells and shipping containers, exposed to broiling sun during the day and freezing temperatures at night, with inadequate food, water, and medical care. Torture of prisoners is routine and deaths frequent. Most prisoners are denied contact with family, lawyers, humanitarian organizations, or other outsiders throughout their captivity. Among the thousands of prisoners held in Eritrea’s over 300 detention centers are adherents of religious groups that the government refuses to recognize as legitimate: Jehovah’s Witnesses, evangelical Christian groups, and reformist elements of the Ethiopian Orthodox Church. Adherents of “unrecognized” religions are arrested and tortured until they renounce their faiths, if then; many who do not recant die in custody.”2
- የኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሠራዊትን አሰልጥነውና አስታጥቀው አንድ ቀን እርማቸውን በ27 ዓመታት ውስጥ ሃገር ገብተው ከወያኔ/ ኢህአዴግ ጋር ሳይዋጉ ኦነግን በቆረጣ ወለጋ አስገብተው ‹‹ኦነግ ሸኔ›› የህዝብ ልጆች እየገደሉ፣ እያፈኑ፣ እያሰሩ፣ ባንኮች እየዘረፉ እንዲኖሩ ያደረጋቸው ስውር እጅ የሻቢያና ወያኔ የፖለቲካ ሴራ ነው፡፡ በትግራይ ክልል ደህሚት ከወያኔ ጦር ጋር ተቀላቅሎ እንዲሰራ ተደረገ፡፡ በአማራ ክልል የግንቦት ሰባት ሠራዊት በብአዲን ሠራዊትነት እንዲመለመልና እንዲሰራ ግን አልተፈቀደለትም፡፡ የአማራውን ክልል መጠናከር ኢሳያስ ሻብያውም፣ ደብረፂዮን ወያኔውም እንዲሁም አብይ ኦነጉም አይፈልጉትም፡፡ ኢዜማዎቹም ብርሃኑ/አንዳርጋቸው!!!
በኢኮኖሚ ዘርፎች ሻብያ ከኢትዮጵያ ህዝብ ዘርፎ ያስቀረው ኃብትና ንብረት ለናሙና፡-
- የቀ.ኃ.ሥና የደርግ መንግሥት ዘመን የነበረው የኢትዮጵያ ባህር ኃይል መርከቦችና የጦር ተዋጊ ጀልባዎች ወዘተ ህወሓት/ ኢህአዴግ የት እንደሸጣቸው መጠየቁ ቀረና ያለ ባህር ባህር ኃይል ይሉናል የድንጋይ ዳቦ ዘመን ፖለቲከኞች፡፡ የኢትዮጵያ የባህር ሀይል (ከ1955 እስከ 1990) ድረስ ነበረ፡፡ ኢምፔሪያል ኢትዮጵያን ኔቪ 81 መርከቦች ነበሩት እነሱም ፓትሮል ቦትስ፣ ቶርፒዶ ቦትስ፣ አነስተኛ ስብመርሲብል (ባህር ሰርጎጂ) ቦትስ፣ ተዋጊ መርከቦች በምፅዋ ወደብ ነበራት፡፡ በወርቃማው ዘመን ቀ.ኃ.ሥ ኮማንደር ኢን ቺፍ የነበሩ ሲሆን፣ ሪል አድሚራል እስክንድር ደስታ ምክትል ኮማንደር ኢን ቺፍ ነበሩ፡፡ የኢትዮጵያ የባህር ኃይል የታጠቀው የጦር መሣሪያ ዓይነትና ተዋጊ የጦር መርከቦች ዲስትሮየር፣ ኬረር፣ ሜትሮ ሃይል ወይም ቀላል ሃይል ወይም አጃቢ ሃይል ከአፍሪካ ሃገራት ዘመናይ እንደነበር በታሪክ ይታወቃል፡፡ የመርከቦቹ እጣ ፈንታ በመለስ ዜናዊ የፖለቲካ ሴራ በሻብያ ኢሳያስ አፈወርቂ ተዘረፈ፡፡
- አሰብ የነዳጅ ድፍድፍ ማጣሪያ ጣቢያ በቀ.ኃ.ሥና የደርግ መንግሥት ዘመን ተገንብተው የነበሩት በሻብያው ኢሳያስ ተዘርፎል፡፡
- ፋብሪካዎች፣እርሻዎችና ሆቴሎች፤- በቀ.ኃ.ሥና በደርግ መንግሥት ዘመን የተገነቡ በኤርትራ ይገኙ የነበሩ መንግሥታዊ ፋብሪካዎች በሙሉ በሻብያ መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ ኃብት ሆኖል፡፡
- ባንኮችና ኢንሹራንሶች በኢሳያስ አፈወርቂ ሃብትና ንብረት መሆናቸው አንሶ፣ በመለስ ዜናዊ ትእዛዝ በብድር የተሰጠ አንድ ቢሊዮን ብር ሳይመለስ ቀርቶል፡፡
- በኤርትራና ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅት በምፅዋ ወደብ ከውጭ የገቡ በብዙ ቢሊዮን ዶላር የወጣባቸው የመንግስትና የግል ባለኃብቶች ንብረትና ኃብት ሁሉ ውኃ በልቶታል፡፡ በተመሳሳይ በወያኔ በግፍ የተዘረፉ የኤርትራዊያን ንብረትና ኃብት የነበሩ ህንጻዎች፣ ቤቶች፣ ፍብሪካዎች፣ መኪኖች፣ ወዘተ የዉኃ ሽታ ሆኖል፡፡
የኤርትራ ህዝብና የኤርትራ የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ጂ 15 ጥያቄዎች አንኮሮቹ ውስጥ፤-በኤርትራ የስብዓዊ መብቶችና የዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ፣ በኤርትራ የፕሬስ ነፃነት እንዲከበር፣ በኤርትራ ህገመንግስት አረቆ እንዲፀድቅ፣ በኤርትራ ህዝባዊ ምርጫ እንዲካሄድ ይጠይቃሉ፡፡ መንግሥት ይሄዳል ይመጣል፡፡ የኢትዮጵያና የኤርትራ ህዘብ ለዝንተ ዓለም አብረው የኖሩ ናቸውና፡፡
ምንጭ (መታየት ያለባቸው ዩቲዩብ ቪዲዬዎች )
1- https://www.hrw.org/report/2011/09/22/ten-long-years/briefing-eritreas-missing-political-prisoners
2-https://www.youtube.com/watch?v=Dujr-s9uQPE / Eritrea: Political Prisoners
3-https://www.youtube.com/watch?v=h61Zfm5uyb0 /Nevsun in Eritrea : Dealing With a Dictator – the fifth estate