April 30, 2020

ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተቆርቋሪ ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ አፍሪቃ ክፍል የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር እስክንድር ነጋ የእጅ ስልክ ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ በፖሊስ ቊጥጥር እንደሚገኝ ዐስታወቀ። ……………. አቶ እስክንድር ኮሮናን ለመከላከል የወጣውን አካላዊ መራራቅ (ማኅበራዊ መራራቅ) ደንብ ሳይጥሱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ያለ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ስልካቸውን እንደወሰደባቸው አምነስቲ ጽፏል።

Amnesty International

AmnestyEasternAfrica @AmnestyEARO

Addis police seized @eskinder_nega‘s phone without court authorization for violating social distancing rules. He fears for his digital security; they’ve unlocked it & have full access. They must immediately return it & stop using #COVID19 as an excuse to infringe upon his rights.

View image on Twitter

255

Twitter Ads info and privacy 156 people are talking about this

የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምሥራቅ አፍሪቃ ክፍል በትዊተር ማኅበራዊ መገናኛ ይፋዊ ገጹ ላይ ዛሬ ያሰፈረው ጽሑፍ፦ አቶ እስክንድር ነጋ «ለዲጂታል ደህንነታቸው» ሥጋት ገብቷቸዋል ይላል። ፖሊስ የእጅ ስልካቸውን ከፍቶ ሙሉ ለሙሉ እንደፈለገ ማድረግ መቻሉን መግለጣቸውንም ጠቅሷል። …………….. ፖሊስ ስልኩን በአፋጣኝ ለባለቤቱ እንዲመልስ አምነስቲ አሳስቧል። ፖሊስ ኮቪድ 19ኝን ሰበብ አድርጎ የሰብአዊ መብታቸውን ከመጣስም ይቆጠብ ሲል ዓለም አቀፍ ድርጅቱ አስጠንቅቋል። …. Source – DW Amharic