logo

Source: https://amharic.voanews.com/a/benishangul-attack-7-31-2020/5525412.html
https://gdb.voanews.com/0398C7EB-BC8F-4CA2-84DA-22CBD6319DA9_cx0_cy5_cw0_w800_h450.png

ሐምሌ 31, 2020

ከቤንሻንጉል ጉምዝ ከ2 ሺህ በላይ ሰው አካባቢውን ለቅቆ መውጣቱ ተገለፀ

ባህር ዳር —በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በጉባ ወረዳ አልመሀል ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩ የአማራ ብሄር ተወላጆች በማንነታችው ላይ ያተኮረ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ዛሬ ተናግረዋል።
የቀበሌዋ ነዋሪዎች ትናንት ከረፋዱ 5 ሠዓት ላይ በእርሻ ማሳዎቻችው ላይ እንዳሉ የታጠቁ ሰዎች ጥቃት ሊያደርሱባቸው ሲሉ ሸሽተው እንዳመለጡና ታጣቂዎቹ ንብረታቸውን በእሳት እንዳወደሙባቸው ገልፀዋል። ከሁለት ሺህ በላይ ሰው አካባቢውን ለቅቆ ለመውጣት መገደዱን አመልክተዋል።

የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል አስተዳደርና የፀጥታ ጉዳዮች ምክትል ቢሮ ኃላፊ ስለጥቃቱ መረጃ አልደረሰኝም ብሏል።

ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ

ከቤንሻንጉል ጉምዝ ከ2 ሺህ በላይ ሰው አካባቢውን ለቅቆ መውጣቱ ተገለፀ

by ቪኦኤ