የዐማራዉ ችግር አንደ ወይራ ሥር የሰደደ እና እንደ ሠርዶ ዉስብስብ ነዉ፡፡
እንደ ወይራ ሥር የሰደደዉን እና እንደ ሰርዶ የተዉሰበሰበዉን ችግር ለመፍታት የችግሩን ይዘቶች እና ዐይነቶች ለይቶ በማወቅ ዓልሞና አቅዶ መስራትን ይጠይቃል፡፡በመሆኑም ይህን ችግር እንፈታለን ብለን የቆምን አካሎች የዐማራዉ ጠላት ማን ነዉ? የጥላቻዉ ምክንያት ምንድን ነዉ? የድርጊቱ አስፈጻሚ ማንነዉ? ፈጻሚ ማን ነዉ? ማስፈጸሚያዉ ምንድን ነዉ? አፈጻጸሙ እንዴት ነዉ?ግቡስ ምንድን ብለን በመጠየቅ ለጥቄዎቹ ተገቢና ትክክለኛ መልሶች ማግኘት አለብን፡፡በመልሶች እርግጠኛ ከሆነ፤ በአጭር ጊዜ እና በረጅም ጊዜ አቅደን በቁርጠኝነት እና በጽናት ችግሩን ለመፍታት መንቀሳቀስ ይኖርብናል፡፡ለዚህ ሁሉ መነሻ እና መድረሻችን ትናንትን ያላወቀ ዛሬን እና ነገን አያዉቅም ፤ወይም የዛሬዉ መሰረት ተናንት ነዉና የኢትዮጵያን ታሪክ በቅጡ ማወቅ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ግዴታ ነዉ፡፡ ታሪክ የአንድ አገር ሕዝብ እና ማኅበረሰብ ማሳያ መስታዉት ነዉ፡፡በመሆኑምረጂሙን የኢትዮጵያ ታሪክ አንጓ የሆኑትን እንቃኛለን፡፡
ኢትዮጵያ የሚለዉ ስም ከግሪክ ቋንቋ የተገኘ ነዉ የሚሉ አሉ፡፡ ለዚህም መነሻ የሚያደርጉት ኢትዮጵያ የሚለዉ ቃል በግሪክኛ ፊቱ በፀሀይ የጠቆረ ማለት እንደሆነ ይስማማሉ፡፡ በኦሪት ዘፍጥረት ኢትዮጰያን ያቀናዉ የካም ልጅ ኩሽ እንደ ሆነ እና፣የአቅኙም ሰዉ ስም ኢትዮጲስ የሚባል ስለነበር፤ኢትዮጵያ የሚለዉ ስም ከኢትዮጲስ የተገኘ እንደሆነ የተለያዩ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ጥንት ከግሪኮች በፊት ኢትዮጵያ በጥንት ግብፃዊያን የኩሽ ምድር ተብላ ትጠራ እንደነበርም ማስረጃዎች እንዳሉ ተዉቋል፡፡
ከክርስቶስ ልደት በፊት በአገሪቱ ከነበሩት መንግሥታት እና ነገሥታት አንዱ ኢትዮጲስ ይባል ስለነበር በሱ ስም ኢትዮጵያ ተባለች የሚሉም አሉ፡፡ጥንት ከግሪኮች በፊት ኢትዮጵያ በጥንት ግብጻዉያን የኩሽ ምድር ተብላ ትጠራ እንደነበር ማሰረጃዎች እንዳሉ ታዉቋል፡፡ በሌላም በኩል አብሲኒያ ወይም የሀበሾች አገር ወዘተ በሚል መጠሪያም ትታወቅ እንደ ነበር ከታሪክ ተመራማሪዎች እስከ ሃይማኖት ሊቃዉንት የተለያዩ መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ይስማማሉ ፡፡
ኢትዮጵያ የሚለዉ መጠሪያ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከስምንት መቶ ዓመታት በፊት የነበረ ለመሆኑ ባለቅኔዉ ሆሜር ኢልያድ እና ኦዲሴይ በተባሉ ድርሰቶች ስለኢትዮጵያ አገራዊነት ጽፏል፡፡በተመሳሳይ ሁኔታ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከአራት መቶ ዓመታት ይኖር የነበረዉ የታሪክ አባት የሚባለዉ ሄሮዶቱስ ስለኢትዮጵያ ጥንታዊ ጽፏል፡፡በአይሁዶች ቶላህ በመባል በሚታወቀዉ በ1400 ዓ.ዓ እንደጻፈዉ የሚነገረዉ የብሉይ ክዳን መጻሀፍ ኦሪት ዘፍጥረት ላይ ኢትዮጵያ ከሌሎች አገሮች ቀድማ በሁለተኛነት ትጠቅሳለች( ዘፍጥረት 2፡13)፡፡
ኢትዮጵያ እጅግ የረዘመ ታሪክ የአላት በርካታ ዉስብስብ እና ዉጣዉረድ የአሳለፈች፤አሁንም ከበርካታ ዉስብስብ ችግሮች ያልተለየች አገር ናት፡፡ ጥንታዊነቷ እና በርካታ ዉስብስብ ችግሮች ያስተናገደች እና እየአስተናገደች ብትሆንም ፤የታሪኳ ፈር ሳይዛነፍ፣ሉዓላዊነቷ ሳይደፈር በዉስጧ አያሌ ማኅበረሰቦችን አካታ ዛሬ ለምትገኝበት ሁኔታ የበቃች ናት፡፡የኢትዮጵያ በህዉርታዊ/መልቲናሺናል)ሕዝብ ታሪካዊ መነሻ እና ማንነት በሚመለከት ዘመናዊ ሥነ ልሳን/የሊንጉስቲክስ ሳይንስ/ እንደአረጋገጠዉ፤በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚገኙ ማኅበረሰቦች የሦስት ጥንታዉ እና አጎራባች የአፍሪካ፣የእስያ እና አዉሮፓ አህጉራት ነባር ሕዝቦች ቋንቋ ተናጋሪዎች ናቸዉ፡፡
ዛሬ እነዚህ ማኅበረሰቦች የአፍሮ- እስያ እና የኢንዶ አዉሮፓ የቋንቋ ቤተሰቦች ተብለዉ በሁለት ታላላቅ የቋንቋ ግንዶችና ምንጮች ይከፈላሉ፡፡ከአፍሮ እስያ የቋንቋ ቤተሰቦች /ዘርፎች/ኩሻዊ እና ሴማዊ ቋንቋዎች በአመዛኙ፤ እማአዊ በሙሉ እና የናይሎ ሰሃራዊ ቋንቋዎች በከፊል የሚገኙት በኢትዮጵያ ጥንታዊ እና ባህዉርታዊ ምድር ነዉ፡፡ ይህም በቅርቡ በአካባቢዉ በተገኙ የአርኪዎሎጂ እና የፓሊዮንቶሎጂ መረጃዎች የኢትዮጵያ የቋንቋ ቤተሰቦች እና ማኅበረሰቦች ባህዉርታዊ እና ጥንታዊነት የበለጠ ተረጋግጧል፡፡
በአለፉት 200 ዓመታት በዐረቢያ፣ በሱዳን እና በግብፅ አጎራባች አገሮች ከአምሳ በላይ በሚቆጠሩ ታሪካዊ ስፍራዎች መካከል በአራቱ የኢትዮጵያ ጥንታዊ የደአማት፣የሳባ፣ የግዕዝና የግሪክ ቋንቋዎች የኢትዮጵያን ጥንታዊነት የሚያረጋግጡ መረጃዎች ተገኝተዋል፡፡ 500 ያህል በድንጋይ ላይ የተጻፉ ጽሁፎች ከከርሰ ምድር በአርኪዮሎጂ ጥናት እና ምርምር ተገኝተዋል፡፡ በነዚህ ጽሁፎች እና በተገኙት ቅሬት አካል መሰረት የግእዝ ቋንቋ ፊደል እና ጽህፈት ጭምር የኢትዮጵያን ጥንታዊ የአዳማት፣ የአኩሱም መንግሥታት እና ሥልጣኔ የነበሩትን በቅርብ ዘመን የአዉሮፓ ምሁራን እንደ ገመቱት ከእስያ ክፍለ አህጉር ወደ እትዮጵያ ገቡ የተባሉት የዉጭ አገሮች ሳይሆኑ የአገሪቱ ነባር እና ጥንታዊ የአፍሪካ ከዚያም የኢትዮጵያ ሕዝቦ ች መሆናቸዉን የተገኙት የአርኪዮሎጂ የምርምር ዉጤቶች አረጋግጠዋል፡፡
በቅርቡ በ20ኛዉ ምዕተ ዓመት መጨረሻ አሥርታት ዉስጥ በአርኪዮሎጂ ቁፈራ በተገኙ የፖሊዮንቶሎጂ መረጃዎችና ጥንታዊ የቅድመ ታሪክ የአጥንት እና የድንጋይ መሳሪያዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደ ተረጋገጠዉ የሰዉ ልጅ ራሱ በህልዉናዉ አካሉ እና አእምሮዉ መሳሪያ አድጎና ዳብሮ በዓለም ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከሰተዉ ከዛሪ ብዙ ሚሊዮን ዓመታት በፊት በስሜን ምስራቅ አፍሪካ ክፍለ አሕጉር በኢትዮጵያ ሽምጥ ሸለቆ ዉስጥ የአዋሽ እና የ ኦሞ ወንዞች እ ናሐሃይቆች ምድር ላይ ነዉ፡፡
ከኢትዮጵያ ምድር መነሻዉን የአደረገዉ የሰዉ ልጅ እና ቋንቋዉ በአለፉት ብዙ መቶ ሽህ ዓመታት ውስጥ በመላዉ ዓለም ላይ በሰፈራ እንደተሰራጨ ዘመናዊ የሊንጉስቲክስ እና የፓሊኦንቶሎጂ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የሰዉን መነሻ እና ስርጭት በሚመለከት አሁን በቅርቡ ሂዳር 1997 ዓ.ም በሦስት የኢትዮጵያ፣የቱርክ እና የአሜሪካ የፖሊኦንቶሎጂ ሳይንቲስቶች የጥናት ዉጤት ይፋ እንደ አደረገዉ በአዋሽ ሸለቆ ዉስጥ በሄርቶ ታሪካዊ ቦታ ላይ የተገኘዉ፤ የጥንት ሰዎች ቅሬት አካል ኢትዮጵያ የሰዉ ዘር መገኛ መሆኗን በድጋሜ አሳይቷል፡፡በአሜሪካ የእስታን ፎርድ እና የሚቺጋን እስቴት ዩንቨርሲቲ የጀኔቲክስ ሳይንቲስቶች በየፊናቸዉ በ51 የልዩ ልዩ አገር ህዝቦች ለደም ናሙና በተመረጡ 938 ሰዎች ላይ በተደረገዉ የደም ምርመራ/ዲኤንኤ/ ጥናት የተገኘዉ ዉጤት እንደአረጋገጠዉ፣የዛሬዉ ዓለም ሰዎች በሙሉ ከዛሬ 160 ሽህ ዓመታት በፊት ከኢትዮጵያ ምድር በሰፈራ እና በፍልሰት በመላዉ ዓለም ላይ እንደተሰራጨ ቢልስ እና ሳይንስ ለዓለም በይፋ አሳዉቀዋል፡፡
(ሳይንቲፊክ ጆርናልስ ኦፍ ኔቸር ኤንድ ሳይንስ የካቲት 21፣ 22/2008ዓ.ም )
በቅርቡ በአለፉት 9 እና 10 ሺህ ዓመታት ዉስጥ በዐባይ ሸለቆ፣ በሜዲትራኒያን ባህር፣ በመካከለኛዉ ምስራቅ፣ እና በዐረቢያ ጥንታዊ እና አጎራባች አካባቢዎች በየዘመናቸዉ፣ በየአካባቢያቸዉ የተነሱት ጥንታዊ የግብፅ፣ የይሁዳ፣ የግሪክ፣ የሮም፣ የፋርስ እና የዐረብ ተከታይ ሕዝቦች እና መንግሥታት በተለይ በንግድ፣በሀይማኖት፣በባህል መንገዶች እና መስኮች በስሜን ምስራቅ አፍሪካ ታሪካዊ እና እስትራቴጂካዊ ክፍለ ሀገር ከኢትዮጵያ ነባር ህዝቦች እና መንግስታት ጋር የመስተጋብር እና የመወራረስ ሁኔታዎች፣ እንቅስቃሴዎች እና ሂደቶች እንደነበራቸዉ በየወቅቱ በጥንታዊ የግብፅ ሀይሮግላፊክስ የዕብራይስጥ፣ የአዳማት፣የሳባ፣የግዕዝ፣የግሪክ፣የላቲን፣የኮፕቲክ እና የዐረብ ቋንቋዎች ተጽፈዉ የተገኙት የታሪክ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
ከ330 እስከ 615 በ285 ዓመታት ዉስጥ በሮማዊያን እና በዐረብ አስተማሪዎች አማካይነት ከመጽሀፍ ቅዱስ እና ከቅዱስ ቁርዓን ጋር ወደ አኩሱም አገር እና ቤተመንግሥት ለመጀመሪያ ጊዜ የገቡት ሦስት የዓለም መለኮታዊ እና አይሀዳዊ የክርስትና፣ የኦሪት እና የእስልምና ሀይማኖት በአንድላይ በአለፉት 1700 ዓመታት ዉስጥ በየፊናቸዉ በየአካባቢያቸዉ የእምነት የድርጅት እና የትምህርት መሰረቶች፣መስሪያዎች እና ምክንያቶች በመሆን ለኢትዮጵያ ጥንታዊ እና በህዉርታዊ የብዙ ሕዝቦች፣ቋንቋዎች፣ሀይማኖቶች፣ ባህሎች አገር ህብረተሰብ እና መንግሥት ህልዉናዊ ክስተት እና አድገት ድምር አስተዋጽኦ እንደአደረጉ በተደረገዉ ጥናት፣ይዘት እና ሂደት በስፋት ይታያል፡፡
እንግሊዛዊዉ ታዋቂዉ የቋንቋ፣የታሪክ እና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ፕሮፌሰር ማርቲን ቤርናል 1897 በአደረገዉ ጥናት እንዲሁም በቅርቡ አዲስ አበባ ተገኝቶ የአዉሮፓ የስልጣኔ ምንጭ አፍሪካ ናት በሚል ከእፎይታ ጋር በአካሄደዉ ትምህርታዊ ቃለ ምልልስ ከ18 እስከ 20 ምዕተ ዓመት የምዕራብ ክርሰቲያን ምሁራን በጀርመን የቋንቋ የታሪክ እና የሀይማኖት ፈለላስፋዎች አመራር በአፍሪካ እና በእስያ ጥንታዊ ሕዝቦች ላይ የነጭ አዉሮፓዊያን የዘር እና የባህል የበላይት ለመገንባት በአካሄዱት ትግል፣ የዘረኝነት አምነት እና ትምህርት ፈጥረዉ በአዉሮፓ እና በአሜሪካ ዓለም ላይ እንደ አስፋፉት፤ ብሎም ጀርመን በሂትለር በይሁዳ ለይ ለተካሄደዉ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንዴት የፖለቲክ መሰረት፣መንገድ እና ምክንያት እንደፈጠሩ በብቃት አሳይተዋል፡፡
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያ ሦስት ታላላቅ መለኮታዊ ዕምነቶችን ተቀብላ የኖረች አገርመሆኗን አዉስተዉ የህዝቧ ታሪከም ከመጽሀፍ ቅዱስ ጋር የተሳሰረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በማያያዝም መጽሀፍ ቅዱስ የሚገልጸዉ ሰዉ ሁሉ ከመካከለኛዉ ምስራቅ የተገኘ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ምዕራባዊ ዓለምም ይህነን ዕምነት ተቀብለዉ እንደሚያስተምሩ ያስረዳሉ፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከደቡብ ዐረቢያ የመጣ ሕዝብ ነዉ የሚሉት እንደ መጽሀፍ ቅዱሱ አባባል አዳም እና ሄዋን የተፈጥሩት በመካከለኛዉ ምስራቅ ዉስጥ ነዉ ከሚለዉ በመነሳት እንደሆነ አስምረዉበታል፡፡
ምዕራባዊያን ምሁራን የሚያስተምሩት በክርስትና፣በእስልምና እና በኦሪት እምነቶች ላይ የተመሰረተዉን ታሪክ ነዉ፡፡መነሻቸዉም በመካከለኛዉ ምስራቅ አካባቢ የአሉ ሕዝቦች ሴማዊያን ስለሆኑ የሴም ቋንቋ ተናጋሪ የሆነ ሕዝብ ሁሉ ከመካከለኛዉ ምስራቅ የፈለሰ ነዉ ብለዉ በማመን ነዉ፡፡በዚህ እምነታቸዉ ለ300 ዓመታት የነጭ ምሁራን ሲያስተምሩ ቆዩ ይህ እምነት ነዉ፡፡የሚፈለገዉ ደግሞ እምነት ሳይሆን እዉቀት ነዉ፡፡እዉቀት የሚጨበጥ የሚዳሰስ ክርክር የሚያስነሳ የመሬት የሕዝብ እና የስፍራ ጥያቄ ስለሆነ ማስረጃ ያስፈልጋል፡፡
ጥንታዊ ስልጣኔ በኢትዮጵያ መገኘቱ ሀቅ ነዉ፡፡ፊደል እና ዘዉድ ኢትዮጵያ ዉስጥ ተገኝተዋል ይህ ደግሞ የሥልጣኔ ምልክት ነዉ፡፡ከዚህ አኳያ በ 1681ዓ.ም ጀርመናዊ የቋንቋ ምሁር ኢዮብ ሉዶልፍ የኢትዮጵያን ታሪክ በሚመለከት አንድ መጽሀፍ ጽፏል፡፡ ይህ ምሁር የኢትዮጵያን ቋንቋዎች ሲመረምር ስምንት ህያዉ የሆኑ እና የሴም ቋንቋዎች የተሰኙትን ማለትም ግዕዝ፣ ተግረ፣ተግርኛ፣አርጎባ ፣ አማርኛ፣ ጉራጌኛ፣ሀረርኛ ፣ ጋፋትኛ ወዘተ የመሳሰሉትን አገኘ በዚህ ግኝት መሰረት ቋንቋዎቹ ከደቡብ ዐረቢያ የመጡ ሕዝቦች ናቸዉ ብሎ አስተማረ፡፡ለምን?
ኢዮብ ሉዶልፍ ክርሰቲያን ነዉ ስለሆነም ሥራዎችን የመሰረተዉ በክርስትና እምነት ላይ ነዉ፡፡በሉዶልፍ ዘመን የአዝጋሚ ለዉጥ ጽንሰ ሀሳብ አልነበረም፡፡ ይህ ሃሳብ የመጣዉ በ19ኛዉ ምዕት ዓመት ነዉ፡፡ ስለዚህ የሉዶልፍ ሥራ የተመሰረተዉ በክርስትና አስተምህሮ ላይ ነዉ፡፡በዚህ የተነሳ የኢትዮጵያ ሕዝብ የእስራኤል እና የዐረብ ወገን ነዉ ከሚለዉ መደምደሚያ ደረሰ፡፡በአጭሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ በአፍሪካ ምድር የሚኖር የአይሁድ እና የዐረብ ዘላን ህዝብ ነዉ ብሎ ፈረጀ፡፡
ከሉዶልፍ ቀጥሎ የተነሱ ምእራባዊያን እና የአይሁድ የቋንቋ እና የሥነ ጽሁፍ ሊቃዉንት በተለይም የጀርመን፣የኢጣሊያን እና የይሁዳ ሊቃዉንት የኢትዮጵያ ሕዝብ ሴማዊ ሕዝብ ነዉ ብለዉ በስፋት አስተማሩ ኢትዮጵያዊያን የተማርነዉ ይህኑ ታሪክ ነዉ፡፡ይህ ማለት ደግሞ ምርጥ የሆነዉ ሴማዊ ሕዝብ ከምድረ ዐረቢያ ተነስቶ ኋላቀር የነበረዉን የአፍሪካ ኩሻዊ ሕዝብ አሰለጠነ እንደማለት ነዉ፡፡
እኛ ታሪካችን ማጥናት እና መመርመር የአለብን በቀኖና ላይ ከተመሰረተ ሀይማኖት ሳይሆን ተጨባጭ መረጃዎች ላይ ነዉ፡፡መረጃ ከለለ ታሪክ የለም ታሪክ የሚኖረዉ መረጃ ሲኖር ነዉ፡፡ ታሪክ ማለት በአለፉት ዘመናት የሰዉ ልጅ እራሱን ከአካባቢዉጋር እያላመደ እና ለራሱ ህልዉና እንዲመቸዉ ተፈጥሮን በመግራት፣ በማምረት፣ በማከፋፈል እና በመጠቀም መካከል የአለዉ መስተጋብር እና ግንኙነት የተጻፉ እና የአልተጻፉ የአለፉ ክንዉኖች ማሳያ የሆነ ተጨባጭ ነገር ነዉ፡፡የሰዎች ሥራዎች የሚነጥሩት ከእዉቀት እንጂ ከእምነት አይደለም እዉቀት የሚገኘዉ ደግሞ ከሰዉ ልጅ ሥራ እና ትምህርት ነዉ፡፡
የኢትዮጵያ ታሪክ ከሦስት መለኮታዊ ሀይማኖቶች አያይዞ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከመካከለኛዉ ምስራቅ የመጣነዉ ማለት ሚዛን የሚደፋ አይሆንም፡፡በተቃራኒዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ከኢትዮጵያ ተነስቶ ዐረቢያን ገዝቷል፡፡ ወደ ቀረዉ ዓለምም ተሰራጭቷል፡፡ለዚህ ማሳያዉ ኢትዮጵያ የሰዉ ዘር መፍለቂያ መሆኗ ነዉ፡፡ በሌላም በኩል፣የኢትዮጵያ ታሪክ ከመካከለኛዉ ምስራቅ ታሪክ ቅድሚያ የአለዉ ሕዝብ ነዉ፡፡ ምክንያቱም የይሁዳ ታሪክ ከአብርሀም ከተነሳን ያለዉ እድሜ 4000 ዓመታት ነዉ፡፡ የአፍሪካ ቀንድ ታሪክ ከይሁድ፣ከሙሴ እና ከኖህ በፊት ነበር ፡፡ሕዝቡም መስራቅ አፍሪካ ዉስጥ ነበር፡፡ሙሴ እራሱ ሲጽፍ በምስራቅ አፍሪካ ያለዉን ሕዝብ ፑንት፤ በሱዳን ያለዉን ሕዝብ ኩሽ፤ በግብጽ የነበረዉን ሕዝብ ግብጻዊ ብሏል፡፡ ስለዚህ እነዚህ ወንድማማች የሆኑ ነባር እና ጥንታዊ ሕዝቦች በአካባቢዉ መኖራቸዉን እንጂ ከዐረብ መምጣታቸዉን የሙሴ ዘገባ አያመለክትም፡፡
ይህን ሀቅ ከተቀበልን በሦስቱም አካባቢዎች በግብጽ፣በኑቢያ እና በኢትዮጵያ ታላላቅ ሥልጣኔዎች ነበሩ፡፡ ነገር ግን ምዕራባዊያን ምሁራን ይህነን እዉነት በመካድ አፍሪካ ሥልጣኔ አልነበረም አሉ፡፡ ጥቁር ሕዝብ አይሰራም የግብጽ፣የኑቢያ እና የኢትዮጵያ ሥልጣኔዎች መጤዎች ናቸዉ ብለዉ አስተማሩ ሥልጣኔዎች የጥቁር ሥልጣኔዎች ሊሆኑ አይችሉም ብለዉ ሰበኩ ደመደሙ ሌላዉንም ሕዝብ አሳመኑ፡፡
አሁን ግን ሳይንስ እና ቴክኒዎሎጂ ከማደጉ የተነሳ የእዉቀት አብዮት ተካሄዶ ምርምር ተጠናክሮ በአርኪዮሎጂ እንደገና ተመረመረ በምድር ዉስጥ ተቀብሮ የነበረዉ ጽሁፍ ተጠና የአርኪዮሎጂ መረጃ አዉሮፓዊያን ታሪክ ብለዉ የአስተማሩትን ተረት ተረት ሆነ፡፡የኢትዮጵያ ቋንቋዎች አገር በቀል መሆናቸዉ ተረጋገጠ፡፡ ከ1955ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ከፍተኛ የአርኪዮሎጂ ጥናት ተካሂዷል፡፡በዚህ መሰረት በጥንታዊ የደአማት፣የሳባ፣የግዕዝ እና የግሪክ ቋንቋዎች የተጻፉ ወደ 500 የሚጠጉ ሰነዶች በኢትዮጵያ ተገኝተዋል፡፡ደአማት ለግዕዝ መነሻ የሆነ ጥንታዊ ቋንቋ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ሰነዶች የሚያሰረዱትም የሴም ቋንቋዎች የአፍሪካ ቋንቋዎች መሆናቸዉን ነዉ፡፡
አዉሮፓዊያን ግን ሴማዊ ፊደል እና ስምንቱ የሴም ቋንቋዎች ማኅበረሰቦች ስለተገኙ ሕዝቦች ከባህር ማዶ ነዉ የመጡት ብለዉ አስተማሩ፡፡እምነታዊ ተጽዕኖም አሳደሩ፡፡አሁን ግን በኢትዮጵያ ከአከሱም ሥልጣኔ በፊት በነበረዉ የደአማት ሥልጣኔ ዘመን ሁለት ፊደላት እንደነበሩ በአርኪዮሎጂ ጥንት እና ምርምር ተረጋግጧል፡፡ከሁለት አንዱ የሳባ ጽሁፍ ሲሆን፤ ይህም ጽሁፍ ሀዉልታዊ እና የቁም ጽሁፍ ነዉ፡፡ሁኖም ይህ ጽሁፍ 100 ዓመታት ያህል ከቆየ በኋላ ጠፍቷል፡፡ ምክንያቱ አይታወቅም፡፡ ከሳባ ፊደል ሌላ ስድ የሆነ ፊደልም ተገኝቷል፡፡ጽሁፉ ተራ ጽሁፍ ሲሆን፤ የዚህ ጽሁፍ ሚስጢር የተገኘዉ በቅርቡ በ1950ዎቹ አሥርተ ዓመታት ነዉ፡፡ የዚህ ጽሁፍ ሚስጢር ታላላቅ ምሁራን የተባሉት ኤኖሌትማን እና ኮነቲሮሲኒ እንኳን ሊያዉቁት ሊረዱት አልቻሉም ነበር፡፡ እነሱም ይህ ጽሁፍ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከተገኘ በኋላ፤ ኢትዮጵያዊያን የአበላሹት የሳባ ፊደል ነዉ አሉ፡፡
አሁን ግን የጥንት ጽሁፍ ሙያተኞች ሲመረምሩት እራሱን የቻለ የደአማት ፊደል ሁኖ ተገኘ፡፡ይህ ፊደል በኋላ ለመጣዉ ለግዕዝ ፊደላት ጽህፈት መሰረት እንደሆነ በአርኪዮሎጂ ጥናት ተረጋግጧል፡፡ይህን ሀቅ እና ዕዉነታ ፈልፍለዉ የአወቁት የዶቹ ተወላጅ አብርሀም ጀሀንድሬዌስ እና የሉክስበርግ ተወላጅ ሮዘር ሸናይደር ናቸዉ፡፡ የዚህን ሚስጢር የአጋለጡት እነዚህ ምሁራን በመጀመሪያ ሌሎች አዉሮፓዊያን የጻፏቸዉን ድርሳናት በሙሉ ከመረመሩ በኋላ አያሌ ጥያቄዎችን ደረደሩ፡፡ ቀጥሎም የአትዮጵያ ፊደል ከዉጭ ለመምጣቱ ማስረጃዉ ምንድን ነዉ ብለዉ ጠየቁ፡፡
ድሬዊስ በ1962 ይፋ እንደ አደረገዉ እስከ አሁን በአዉሮፓዊያን ስለኢትዮጵያ የተነገረዉ ታሪክ ስህተት የአለበት መሆኑን በሚገባ አረጋገጠ፡፡በመጨረሻም ኢትዮጵያ ዉስጥ የተገኘዉ የደአማት ፊደል አገር በቀል መሆኑን ድሬዌስ እና ሸናድር በትክክል አረጋገጡ፡፡ሁለቱ ምሁራን የደረሱበትን ግኝት ትክክል መሆኑን ዓለምን አሳመኑ፡፡እርግጥ የሳባ ፊደል ኢትዮጵያ ዉስጥ ተገኝቷል፡፡ ነገር ግን ከሱ በፊት ለዛሬ ኢትዮጵያ ቋነቋዎች እና ስልጣኔ መሰረት የሆነዉ የደአማት ፊደል የተገኘዉ በኢትዮጵያ ምድረ ነዉ፡፡ፊደሉ ከኢትዮጵያ ዉጭ በሌላ ዓለም አልተገኘም፡፡ አለመገኘቱንም የቋንቋ ሳይንስ እና የአርኪዮሎጂ መረጃዎች አረጋግጠዋል፡፡
በቋንቋ ሳይንስ እና መረጃዎች እዉነታ መሰረት ፊደሉ በታዳጊነት ደረጃ ላይ የነበረ ቢሆንም ለግዕዝ ቋንቋ ፊደላት ጽሁፍ መሰረት እና መነሻ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ በኋላ ግን እያደገ በመሄድ እና አናባቢ ምልክቶችን በመጨመር የግዕዝ ፊደል ሁኖአል፡፡በዚህ መሰረት እስከ አሁን የአለዉ ስልጣኔ የሚጀምረዉ ከአኩሱም ስልጣኔ 500 ዓመታት በፊት ከነበረዉ ከደአማት መንግሥት ነዉ፡፡የደአማት ሥልጣኔ ከመጀመሩ በፊት በአፍሪካ ቀንድ የፑንት ስልጣኔ ነበር፡፡የፑንት መንግሥት ከግብጽጋር ከ2800 እስከ 1000 ዓመተ ዓለም ድረስ ለ1800 ዓመታት ያህል የጠበቀ የንግድ ግንኙነት ነበረዉ፡፡ በዚህ ወቅት ተስሎ የተገኘዉ ሥዕል የዛሬ ሱማሌዎችን፣ኦሮሞዎችን ፣ ትገሬዎችን እና አፋሮችን ወዘተ የሚመስል ገፅታ አለዉ፡፡ ሥዕሉ አነዚህ ሕዝቦች በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የሚኖሩ ጥንታዊ ሕዝቦች መሆናቸዉን ያሳያል፡፡ ይህ ከዛሬ 7000 ዐመታት በፊት የነበረ ሥዕል ኢትዮጵያ ከጥንት ግብፃዊያን ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንደነበራት ያሳያል፡፡
በስሜን ኢትዮጵያ ያልተቋረጠ ዘመናዊ መንግሥት የጀመረዉ ከደአማት ዘመን ሲሆን፣ ከዚህ በኋላ የአኩሱም መንግሥት በተከታታይም የአገዉ እና የአማራ መንግሥታት በመፈራረቅ ኢትዮጵያን ማስተዳደራቸዉ ግልጽ ነዉ፡፡ በደቡብም እንደዚሁ ሁር እና ሃድያ የሚባሉ የመጀመሪያ ሕዝቦች እና መንግሥታት ነበሩ፡፡ እስልምና ወደ ኢትዮጵያ ከገባ በኋላ አያሌ መንግሥታት ተሰፋፍተዋል፡፡በዚህ መሰረት ለመንግሥታት መበራከት የኦሪት፣ የክርስትና እና የእስልምና እምነቶች ምክንያት ሁነዋል፡፡ሃይማኖት ከጥንት ጀምሮ ከመካከለኛዉ መስራቅ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንደነበረዉ ያሳያል አርኪዮሎጂ የሚመሰክረዉ ይህን ሀቅ ነዉ፡፡ ሀቁ ይህ ከሆነ ደግሞ ከ50 ዓመታት በፊት ስለ ኢትዮጵያ የተጻፉት ታሪኮች ሁሉ የፖለቲካ ተረቶች ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡መነሻቸዉም ጥቁር ሕዝብ የሥልጣኔ ፈጣሪ ሊሆን አይችልም የሚል የትምክህተኛ መላምት ነዉ፡፡ የሚገርመዉ ነገር ግን እስከ ዛሬ ድረስ እኛ ኢትዮጵያዊያን ይሕነን ተረት ተቀብለን ማሰተጋባታችን ነዉ፡፡አሁን እዉቀት በሰፈነበት ዘመን ፈረንጆች የአሉትን ተቀብሎ ማስተጋባቱ የሚያዋጣ ነገር አይደለም፡፡ የአርኪዮሎጂ መረጃ የሚያሳየዉ የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ምንጭም ፣መነሻም፣ባለቤቱም ኢትዮጵያዊያን መሆናቸዉን ነዉ፡፡
አዉሮፓዊያን የመነሻ እና የማንነት ችግር አለባቸዉ፡፡ አዉሮፓ የማንነት ችግር የአለበት አህጉር ነዉ፡፡ ግብፆች የዓለም መንግስት በነበሩበት ጊዜ ፊንቃዊያን የዓለም አስተማሪዎች በነበሩበት ወቅት ባቢሎንያዊያን የዓለም ህግ አስተማሪዎች ነበሩ፡፡ በዚህ ወቅት የአዉሮፓዊያን ሥልጣኔ አልነበረም፡፡ ከዘመናት በኋላ ግን ግሪኮች ተነስተዉ ወደ ግብፅ ተጉዘዉ ሃይማኖትን እና የሀይማኖት ሥርዓትን፤ ጂኦሜተሪን እና ኪነጥበብን ከግብፅ ሊቃዉንት ተማሩ፡፡ ከፊንቃዊያንም የተለያዩ ጥበቦችን ተምረዋል፡፡
በዚህ መክንያት ግሪካዊያን ሰለጠኑ፡፡ ሮማዊያንን አጠቁ፡፡ እስልምና ሲነሳ ግን ታጠፉ፡፡ከዚያን በኋላ ምዕራብ አዉሮፓ ዉስጥ ከማዕከላዊ እሰያ የመጡ ባራባሪያን የተባሉ ወራሪ ዘላኖች የግሪክን እና የሮማን ሥልጣኔ አጥንተዉ የራሳቸዉን አዲስ ክርሰቲያናዊ ሥልጣኔ መሰረቱ፡፡ከዚያም መስፋፋት ጀመሩ፡፡ ነገር ግን የአስልምናን እንቅስቃሴ መቋቋም አልቻሉም፡፡የመስቀል ጦርነት የሚባል ዘመቻ አወጀዉ ለ300 ዓመታት ተዋግተዉ ተሸነፉ፡፡ ከዚያም የተነሳ የጥቁር ዘር አኩይ ነዉ፤ የዐረብ ዘር እርጉም ነዉ፤ እስልምና ማለት ባርነት ነዉ ብለዉ ሰበኩ፤ አስተማሩ፡፡
ከዘመናት በኋላ ግን አዉሮፓዊያን ሳይነስ እና ቴከኒዮሎጂን አሰፋፍተዉ በየብስ የአቃታቸዉን በባህር ተጉዘዉ ዓለምን በቅኝ ግዛት ያዙ፡፡ አፍሪካን የባሪያ ገበያ፤ የምዕራባዊ ንፍቀ ክበብ አህጉራትን አወስትራሊያን
እና ኒዉዝላንድን መኖሪያቸዉ አደረጉ፡፡ከዚህ በኋላ የማንነት ጥያቄ ተነሳ፡፡ ጀርመኖች ፣አንጉሎ ሳክስኖች እና ፍራንኮች ኋላቀር( ባርባሪያንስ) ስለነበሩ ከዚያ የተገኘ ሥልጣኔ ስለ አልነበራቸዉ ፊታቸዉን ወደ ግሪክ ሥልጣኔ አዞሩ፡፡ ይህነን የአደረጉት የማንነት ጥያቄ ለመመለስ ነዉ፡፡ ከሮማኒያን ህግን ከግሪኮች ዲሞክራሲን ወሰዱ፡፡ ያም ሰለ አልበቃቸዉ ክርስትናን አጠናከሩ፡፡
የግሪክ ሥልጣኔ ሲመረመር ከግብፅ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ሁኖ አገኙት፡፡ ግን አምኖ ለመቀበል አልፈቀዱም፡፡ ምክንያቱም ባሪያ አድርገዉ የገዙትን እና የሰዉ ዘር አይደለም ብለዉ የካዱትን ህዝብ የሥልጣኔ ምንጭነዉ ብለዉ መቀበል አዳገታቸዉ፡፡ ሁኖም ሦስት የጥቁር ህዝብ ሥልጣኔዎች አግኝተዋል፡፡ እነሱም የግብፅን ፣የኑቢያን እና የአኩሱም ሥልጣኔዎች ናቸዉ፡፡እኒህን ሥልጣኔዎች አፍሪካዊ ሥልጣኔዎች ናቸዉ ብለዉ ለመቀበል አልፈለጉም፡፡ የህን ያልተቀበሉበት ምክንያት፣ የሚያካሂዱትን የባሪያ ንግድ የሚቃረን ስለሆነባቸዉ ነዉ፡፡ይህም አዉሮፓዊያን ከፍተኛ አጣብቂኝ ዉስጥ ከተታቸዉ፡፡አዉሮፓዊያን ከገቡበት አጣብቂኝ ለመዉጣት፣በስልጣኔ እና እድገት ስም የፈጠራ ታሪካቸዉን አስተማሩን፡፡ የነፃ ትምህርት እድልም ሰጡን እኛም ያስተማሩነን ፣የነገሩነን ምንም ሳንጠራጠር ተቀበልን፡፡ይህነን እኛም ለልጆቻችን አስተማርን፡፡ ዕዉቀት እየሰፋ ሳይንስ እና ቴክኒዎሎጂ እዳበረ ሲሄድ ዕዉነቱ ከሀሰቱ እየተገለጠ መጣ፡፡ የአርኪዮሎጂ እዉቀት ዕያደገ መምጣት፣ቀደም ሲል የሰዉ ልጅ እንደ ሰዉነት የተቀበላቸዉን ነገሮች መለስ ብሎ እንዲያጠናቸዉ እና ሐቁን ከዉሸቱ እንዲለይ መንገድ አሳየዉ፡፡ሥነ-ልሳን በበኩሉ የሴም ቋንቋዎች ወደ መካከለኛዉ ምስራቅ የሄዱት ከአፍሪካ ቀንድ አከባቢ ተነስተዉ እንደሆነም አሳየ፡፡ በዚህ መሰረት ማስረጃዎች የሚያረጋግጡት የኢትዮጵያ ቋንቋዎች አገር በቀል መሆናቸዉን እንጂ፣ ከዉጭ የመጡ መጤ አለመሆናቸዉን በይፋ እንዲታወቅ ሆነ፡፡ የኢትዮጵያ ቋንቋ እና ማህበረሰብ አገር በቀል እንጂ አንደም ከዉጭ ወደ ዉስጥ የገባ አለመኖሩን ጥናቶች አረጋገጡ፡፡
የሚያስገርመዉ ነገር በሌላዉዓለም ዘር ሲጠፋ በአፍሪካ ቀንድ ግን የጥንቱ ፑነታዊያን ደአማታዊያን ሆኑ፤ ደአማታዊያን ደግሞ አኩሱማዊያን ሆኑ፤ እንጂ አልጠፉም፡፡ ፈረንጆች ያስተማሩን ግን በተቃራኒዉ ነዉ፡፡ ለመሆኑ በመካከለኛዉ ምስራቅ ያልነበረ ቋንቋ እንዴት ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ይችላል፡፡በፓሊኦንቶሎጂ መረጃና ትምህርት መሰረት የሰዉ ዘር መገኛ ምንጭ ባቢሎን እና መካከለኛዉ ምስራቅ ሳይሆን የአፍሪካ አህጉር ነዉ፡፡
እንደ ይሁዳዊያን እና አዉሮፓዊያን የሃይማኖት ትምህርት ከሆነ የአለምታሪክ ከ8000 ዓመታት አይበልጥም ምክንያቱም ትምህርታቸዉ በሀይማኖት ላይ የተመሰረተ ስለሆነ የምድርን እድሜ ከ8000 ዓመታት በታች ያደርገዋል እና ነዉ፡፡ በኢትዮጵያ የተገኘዉ የድንቅነሽ እድሜ ግን ከ3 ሚሊዮን ዓመታት በላይ ነዉ፡፡ የሰዉ ልጅ የተገኘዉ በአዋሽ አካባቢ ነዉ አዋሽ ደግሞ የኢትዮጵያ ወንዝ ነዉ፡፡ ዩኔስኮ ስለ አፍሪካ ታሪክ በ 8 ተከታታይ ቅጾች በአሳተመዉ ጽሁፍ የሰዉ ዘር መገኛ አፍሪካ መሆኑን በሚገባ አብራርቷል ተቀብሎታል፡፡ የጀርመኖች እና የኢጣሊያን ምሁራን አሁን የአፍሪካን የሰዉ ዘር ምንጭነት ይቀበላሉ፡፡ የሁለት ሚሊዮን እድሜ የአለዉ የድንጋይ መሳሪያ ከአዲስ አበባ 50 ከሎሜትር እርቀት ላይ በመልካ ቁንጥሬ ተገኝቷል፡፡በአፋር ምድር የተገኘዉ የድንጋይ መሳሪያ ደግሞ የአራት ሚሊዮን ዓመታት እድሜ ያለዉ ሲሆን፤ ይህም የቤተክርሰቲያን ዕፅዋት፣ አዝዕርት፣ አራዊት እና የሰለጠነ ሕዝብ የተገኘዉ በዚሁ ነዉ፡፡
የተከዜ፣ የአዋሽ፣የዐባይ፣የቀይባህር፣የኦሞ፣የዋቢሸበሌ የዳቡል፣ ወዘተ ወንዞች የሚገኙት በዚህ አካባቢ ነዉ፡ ፡በዚህ አካባቢ የሚገኘዉ ሕዝብ በሚያደርገዉ እንቅስቃሴ በጦርነት በጋብቻ እረስ በርስ የተወራረሰ ነዉ፡፡ ከሥልጣኔዉም ትልቁ ነገር የመንግሥት ምስረታ ነዉ፡፡በዚህ እረገድ የፑንት መንግሥት ከየትኛዉም አገር በፊት መንግሥት ከመሰረተዉ የጥንቱ የግብጽ መንግሥታት ጋር ለ1800 ዓመታት ያህል የጠበቀ ግንኙነት ነበረዉ፡ የአፍሮ እሰያ ቋንቋዎች መገኘት አብዮታዊ አስተሳሰብን አምጥቷል፡፡ የዚህ ግኝት ባለቤት አሜሪካዊ ፕሮፌሰር ጆሴፍግሬን በርግ ናቸዉ፡፡የአፍሮ እስያ የቋንቋ ቤተሰብ የግብፅ ፣የበርበር፣የስሜን አፍሪካ፣የምዕራብ አፍሪካ፣ኩሻዊ፣ ሴማዊ፣ እማዊ እና ናይሎቲካዊ የተባሉት የኢትዮጵያ ቋንቋዎችን ያጠቃልላል፡፡እነዚህ ቋንቋዎች
የአፍሪካ እና እስያ ጥንታዊ ተዛማጅ ቋንቋዎች ናቸዉ፡፡የሴም ቋንቋዎች በኢትዮጵያ በደቡብ ዓረቢያ እና በመካከለኛዉ ምስራቅ ይገኛሉ፡፡ኩሻዊ ቋንቋዎች የሚኙት በኢትዮጵያ ሲሆን፤ ሌሎች የኩሽ ቋንቋዎች በጎረቤት አገሮች ይገኛሉ፡፡24 የሚሆኑ የኩሽ ቋንቋዎች በኢትዮጵያ ይገኛሉ፡፡የእማዊ ቋንቋዎች የሚኙት በኢትዮጵያ ብቻ ነዉ፡፡ ናይሎቲክ ቋንቋዎች በኢትዮጵያ እና በጎረቤት አገሮች ይገኛሉ፡፡ እነዚህን ቋንቋዉች የሚናገሩ ህዝቦች ጥንታዊ ያን እና ተዛማጅ ናቸዉ፡፡ ህዝቦቹ በዘር፣በቦታ፣በስፍራ በጊዜ ተወራርሰዋል፡፡ ነባር እና የአካባቢያዊ ነዋሪዎችም ናቸዉ፡፡
ኩሻዊ ቋንቋ የሚወክለዉ ሦስት ጥንታዊ ህዝቦችን ሲሆን፤ ይኸዉም በአፍሪካ ቀንድ ፑነታዊያን በላይኛዉ የዐባይ ሸለቆ ኑቢያን፤ በታችኛዉ የዐባይ ሸለቆ ግብጻዊያንን ነዉ፡፡ ከነዚህ ዉስጥ የኑባዊያ ቋንቋ ጠፍቶ አገሩም የዐረቦች አገር ሁኖአል፡፡ግብፅም እንደዚሁ የዐረቦች አገር ሁኖአል፡፡ ዛሬ የነዚህን የኩሽ ቋንቋዎች የሞተ ወኪል ኢትዮጵያ ናት፡፡የፑንት፣ የግብፅ እና የኑቢያ ወራሽ የሆነዉ ያልጠፋ አገር እና ሕዝብ የሚገኘዉ አፍሪካ ቀንድ ነዉ፡፡ቋንቋ በኢትዮጵያ የዘር መለያ እና የማንንት መገለጫ እየሆነ መጥቷል፡፡በኢትዮጵያ አዲስ የፖለቲካ ሥልት አዲስ የኢኮኖሚ ሥርዓት እየተመሰረተ ነዉ፡፡ ለዉጥ እየተካሄደ ነዉ፡፡ ይህነን ለማድረግ የሚያስቸሉ መረጃዎች ተገኝተዋል አዲስ የታሪከ አጠናን ዘዴ ተፍጥሮአል፡፡
ቋንቋ የሀገር፣ የብሔር፣ የብሔረሰብ እና የማኅበረሰብ መለያ ተደርጓል፡፡ በኢተዮጵያ በአለፉት አርባ አምሳ ዓመታት የብሔረሰቦች ዐብዮት እየተካሄደ ነዉ፡፡ የብሄርብሄረሰብ ዐብዮት ማለት የቋንቋ፣ የታሪክ ፣ የሀይማኖትእና የባህል እንቅስቃሴ መግለጫ ማለት ነዉ፡፡በአሁኑ ዘመን የአረኪዮሎጂ፣ የሥነ ልሳን እና የፓሊኦንቶሎጂ መረጃዎች ከኛ ጋር ተሰልፈዋል፡፡ የአፍሮ እስያ ቋንቋ ቤተሰብ መገኘት ከዚህ ቀደም የነበረዉን ታረክ ሽሯል፡፡ቀድሞ የነበረዉ ታሪክ ጥንታዊ የአይሁድ አስተማሪዎች እና ጸሀፊዎች በጻፉት ድርሰት ላይ የተመሰረተ ነዉ፡፡ ታሪኩም ከእምነት ጋር የተቆራኘ ነዉ ፡፡መጽሀፍ ቅዱሳዊ ታሪክ ነዉ፡፡ የአዉሮፓ ታሪክ ጸሀፊዎች ያስተጋቡት የነበረዉ ይህነን ታሪክ ነዉ፡፡ በዚህ የተነሳ ነዉ የሴም ቋንቋ መነሻዉ መካከለኛዉ ምስራቅ ነዉ የተባለዉ፡፡
አዉሮፓዊያን በበኩላቸዉ የኢንዶ-አዉሮፓ ፣ግሪክ እና ላቲን ቋንቋዎችን አቅፈዉ ተነሱ፡፡ በዚህም ምርጥ ዘር ነን እና ዓለምን መገንባት አለብን አሉ፡፡ ከሰዉ ዘር ሁሉ ምርጥ የሆነዉ የአርያን ዘርነዉ የሚል ፍልስፍና አመጡ፡፡አፍሪካን ባሪያ አድርገዉ መግዛት ያዙ፡፡ የአፍሪካ ህዝቦችን ሥልጣኔ ካዱ፡፡ ይህም ለባሪያ ንግድ እንዲያመቻቸዉ ነዉ፡፡የግብፅን ሥልጣኔ መካድ ሲቸግራቸዉ ደግሞ፤ ግብፅ ጥቁር አይደለም ነጭ ነዉ አሉ ፡፡ ኑቢያም ነጭ እንጂ ጥቁር ሕዝብ አይደለም አሉ፡፡ የኢትዮጵያን ስልጣኔ አፍሪካዊነት ለመካድ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጭ እንጂ ጥቁር አይደለም አሉ፡፡አዉሮፓዊያን በማወናበድ ላይ ሳሉም፤ ሂትለር ዘር ለማጥፋት ተነሳ አዉሮፓዊያን አፈሩ፡፡ ይህን ሁሉ ጣጣ ያመጡት የሰዉ ዘርን ጥላቻ እና ንቀት ሲሰብኩ የነበሩት ፈላስፋዎቻቸዉ ናቸዉ፡፡
ዓለምን እንደገና ለመቀራመት በለኮሱት የሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ወቅት መከራን ተጋቱ ጥቁር ሕዝብ ሰባዊ ፍጡር አይደለም ብለዉ ሲሰብኩ የነበሩ ጀርመኖች እራቁታቸዉን ቀሩ፡፡የዘረኝነት ፍልስፍናቸዉ እራሳቸዉን መልሶ ሲያቃጥላቸዉ ፤ዛሬ የሰዉ ልጅ ሁሉ አኩል ነዉ፡፡ ሰባዊ መብት ይከበር እያሉ ማስተማር ጀመሩ፡፡ ከአዉሮፓ ዘር ዉጭ ያለዉ ህዝብ ሰባዊ ፍጡር አይደለም እንዳላሉ ሁሉ ዛሬ ለሰዉ ዘር ዲሞክራሲያዊ መብት ተሟጋች ሆኑ፡፡ ይህን እንዲቀበሉ የተገደዱት በጥቁሮች የጠነከረ ትግል እና የቴክኖሎጂ እድገት መስፋፋት የተደበቀዉን ዕዉነት ገላልጦ በማሳየቱ ነዉ፡፡
በቋንቋ እረገድ የነበረዉ መላምት ዉድቅ ሁኖባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያን ቋንቋዎች በኢንዶ- አዉሮፓ እና በአይሁድ ቋንዎቸወ ዉስጥ ማስቀመጥ አልቻሉም፡ ፡ የአሜሪካ ፕሮፌሰሮች የደርሱበት ጭብጥ የእሰያ እና የአፍሪካ ቋንቋዎች ተዛማጅ መሆናቸዉን ነዉ፡፡
ኢትዮጵያ ዉስጥ የአሉ ቋንቋዎች አገር በቀል እንጂ ከዉጭ ያልመጡ መሆናቸዉ ታዉቋል፡፡ ይህ ደግሞ አሁን ለተያያዝነዉ አገር ግንባታ በጣም ጠቃሚ ነዉ፡፡ ሴማዊ ፣ኩሻዊ፣ ናይሎቲካዊ እና እማዊ ህዝቦች ነባር እና ኢትዮጵያዊ ህዝቦች ናቸዉ፡፡ማስረጃዎች የሚያረጋግጡትም አንድም መጤ የሆነ ህዝብ ኢትዮጵያዊ እንደለለ ነዉ፡፡ አኛ መመራት የአለብን በሳይንስ መረጃ እንጂ፤ በእምነት ብቻ መሆን የለበትም፡፡ ታሪክን የምናዉቀዉ በመዳሰስ ነዉ ዘመኑን፣ ሕዝቡን እና ሥፍራዉን ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ ይህን ለማድረግ የሚረዱን ደግሞ የፓሊኦነቶሎጂ እና የሥነ ልሳን መረጃዎች ናቸዉ ፡፡
በነዚህ መረጃዎች አማከኝነት የኢትዮጵያን መነሻ እና ማንነት ማወቅ እንችላለን፡፡ ኢትዮጵያዊያን ከጥንት ጀምሮ አሉ ፡፡ታላላቅ የነበሩትን የሮማን እና የፋርስን ሥልጣኔዎችን የደመሰሰዉ የዐረብ እንቅስቃሴ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ተወዳጀ እንጂ ኢትዮጵያን አላጠፋም፡፡ ቱርኮች እና ፖረቹጋሎች ኢትዮጵያን ለማጥፋት ሞክረዉ ነበር ግን ተሸነፉ፡፡ቅኝ ገዥዎችም ሞክረዉ ነበር ግን አደዋ ላይ ተጠቁ፡፡
ፋሽዝም ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ለማድረግ ጦርነት ገጥሞ ተሸነፈ፡፡ ኢትዮጵያዊያንም የአካሄዱት የአምሳ ዓመታት ዐብዮት የሕዝቡን አንድነት አጠናከረ እንጂ አላፈረሰም፡፡ ይህ አካባቢ ህልዉናዉን ጠብቆ የሚኖር ለዩ ችሎት ያለዉ ስፍራ ነዉ፡፡ ሕዝቡ ጥንታዊ ነዉ፡፡ ኋላ ቀር መሆኑ ታሪኩን የሚያዛባ ነገር አይደለም፡፡ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዉሀ ጋን ናት፡፡ የኢትዮጵያን ዉሀ የኑቢያን እና የግብፅን ሥልጣኔ አፍርቷል፡፡ ኢትዮጵያዊያንም አኑሮናል፡፡ የኢትዮጵያ ተራሮችም ሕዝቡ ጠላቶቹን ለመከላከል ታላቅ አስተዋጽኦ አድረገዋል፡፡ኢትዮጵያ በየአይነቱ ሀብት አላት፡፡ የደጋ፣ የወይና ደጋ፣ የቆላ እና የበርሀ የአየር ንብረቷ ለብዙኃን ሕይወትአጅግ በጣም ተስማሚ በመሆኑ በየዓይነቱ ዕፅዋት አዝዕርት፣አራዊት እና እንስሳት ይገኙባታል፡፡ ይህ ደግሞ ለሕዝብ እንቅስቃሴ ዉስጣዊ ፍልሰትን እና ዉህደትን በማስከተል የሕዝቦች መስተጋብርን እና መወራረስን ፈጥሯል፡፡
ፕሮፌሰር ማርቲን ቤርናል ባህዉርታዊ የሆነ ቋንቋ ጥንታዊነቱን ማመልከቱ እርግጥ ነዉ፡፡ የተማከለ እና የተደራጀ ቋንቋ ደግሞ ዘመናዊ መሆኑ እርግጥ ነዉ ፡፡እስከ ዛሬ ድረስ ያለዉን ታሪክ የጻፉት ፈረንጆች እና ዐረቦች ናቸዉ፡፡ሁላችንም ባዕዳን የጻፉትን ነዉ የምናስተጋባዉ፡፡ በአሁኑ ዘመን ታሪክ ለመጻፍ አርኪዮሎጂ፣ ፓለኦንቶሎጂ ፣ኤፒግራፌ እና የተለያዩ የትምህርት ዘዴዎች ቋንቋዎች ማወቅ ያስፈልጋል፡፡እስከ አሁን የነበረዉ የኢትዮጵያ ታሪክ ዜና መዋእለ ገድለ ቅዱሳን ገድለ ሰማዕታት ነዉ፡፡ የጻፉት የቤተክህነት እና የቤተመንግስት ባለሙያዎች ናቸዉ፡፡የተጻፈዉ የመኳንንት፣የመሳፍንት እና የነገሥታት ታሪክ ነዉ፡፡ ይህ ዛሬ ዓለም ከደረሰበት የታሪክ አመዘጋገብ ደረጃ ሲታይ የሚጎድለዉ ነገር ይኖራል፡፡ሆኖም የፊቱ ከለለ የኋላ የለም እና፣ለተሟላ ታሪክ አመዘጋገብ በመነሻነት የሚያበረክተዉ ድርሻ ከፍተኛ ነዉ፡፡ ምክንያቱም የህዝብን እዉነተኛ ታሪክ በመረጃ ከዚያም አልፎ በማሰረጃ መጻፍ እንዳለበት ይታመናል፡፡በኢትዮጵያ ዓለም አቀፋዊ የጥናት ጉባኤዎች ላይ በየጊዜዉ አዳዲስ ሃሳቦች እና ግንኙነቶች ይቀርባሉ፡፡
ረጅሙኢትዮጵያ ታሪክ እንደሚያሳየን፤ ድንበሯ በስተስሜን ግብፅን ተሸግሮ ደቡብ ዐረቢያን በርካት የምስራቅ አፍሪካ አካባቢዎችን የአካተተ እንደነበር የታሪክ መዛግብት ይናገራሉ፡፡በ24 ዓመተ ዓለም ሮማዊያን ከግብፅ በመነሳት በዐረቢያ ላይ የመጀመሪያ ወረራ አካሄዱ፡፡በዚህ ወረራም በዘመነ ክርስትና ከ105 እስከ 108 የሮማዊያን የዐረቢያ አዉራጃ ተመሰረተ፡፡ይህም ዐረቢያ በአፍሪካ፣ በአዉሮፓ እና በሩቅ እስያ አገሮች መካከል እስትራቴጂያዊ የዓለም ንግድ መነኻሪያ መንገድ እና ኬላ ሆነ፡፡ሁለቱ ሃያላን ማለትም የሮም እና የፋርስ መንጋሥታት በአካባቢዉ በንግድ፣ በእስትራቴጂ እና በሃይል ሚዛን ጉዳይዎች ላይ ለረጅም ዘመን በአላንጣዎች ሁነዉ ዘለቁ፡፡
ኢጣሊያዊ የኢትዮጵያ ታሪክ ተመራማሪ እና ጸሐፊ ሙሴ ኮንቲሮሲኒ በ1872 እስከ1949 የሰነድ ማስረጃ ተቅሶ እንደ አስረዳዉ፤በ 130 ዓ.ም በዐረቢያ አንድ የኢትዮጵያ መንግስት እንደራሴ ንጉስ ደቡብ ዐረቢያን ያስተዳድር እንደ ነበር አረጋግጧል፡፡ ቀጥሎም ከ 175 እስከ 225 ዓ.ም ድረስ በሳባ ቋንቋ እና ፊደል በድንጋይ ላይ የተጻፈ በየም አገር፣ ከማሬብ ጥንታዊ የሳባ ከተማ የተገኘዉ፣ ብዙ የዐረብ መንግሥታት ዜና መዋዕሎች፣ የሃበሾች እና የአኩሱማዊያን ነገሥታት ገደረት፣ ዋዜባ እና አደባ የተባሉ ደቡብ ዐረቢያን ይገዙ የነበሩ የኢትዮጵያ ነገሥታት ታሪክ አሁን በዘመናችን በአርኪዮሎጂ ጥናት እና ምርምር መገኘቱ ተረጋግጧል፡፡ በተጨማሪም በሦስተኛ ምዕተ ዓመት መጀመሪያ አጋማሽ በኢትዮጰያ በመዳብ ዘንግ ላይ በግዕዝ ቋንቋ እና ፊደል የተጻፈ እና የአኩሱማዊያን ንጉስ ገደር የሚል አንድ ታሪካዊ ጽሁፍ በቅርቡ በስሜን ምስራቅ ትግራይ ከአንድ ጥንታዊ ስፍራ ተገኝቷል፡፡
በደቡብ ዐረቢያ የሳባ ጽሁፍ የሀበሾች እና የአኩሱማዊያን ንጉስ ገደር ተብሎ የተጠቀሰዉ እና በኢትዮጵያ በገዕዝ ፊደል የአኩሱማዊያን ንጉስ ገደርብሎ የገለጸዉ፤ በሁለት የተለያየ ስፍራዎች የተጠቀሰዉ ገደር የኢትዮጵያ ንጉስ እንደሆነ በዘመኑ ቋንቋ እና ታሪክ አዋቂ ምሁራን አስረድተዋል፡፡ በዐረቦች ሀበሻ የሚሉት የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያዊያን ስም በታሪክ ሰነድ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጽፎ የተገኘዉ በ183 ዓ.ም በዐረቢያ በሳባ ቋንቋ እና ፊደል በተጻፈ በአንድ የሄምዳኑ አረብ መሳፍንት ዜና መዋዕለ ነዉ፡፡ሀበሻ በምስራቅ አፍሪካ ለምትገኘዉ ኢትዮጵያ የተሰጠ የዐረቦች የወል ስያሜ ነዉ፡፡መሰረታዊ ትርጉሙ ዐረብ ያልሆነ የአፍሪካ ሰዉ ማለት ነዉ፡፡ በኢትዮጵያ ምድር እና ቤተመንግስት ከ550 እስከ 13000 ዓ.ምድረስ የታሪክ ማስረጃ ሰነድ ከአገር ዉጭ የዐረብ ሙስሊሞች ብቸኛ ምንጭ እንደሆኑ ታዉቋል፡፡ ለኢትዮጵያዊያን እስልምና መለኮታዊ ሀይማኖት ብቻ ሳይሆን የታሪክ ቅርስ እና ዉርስ ነዉ፡፡
የኢትዮጵያ የመጨረሻዉ እማዊ እና የመጀመሪያዉ ክረስቲያን ንጉሥ የሆነዉ አጼ ኢዛና ከ320 እስከ 360ዓ.ም ከምዕራብ ኑቢያ አስከ ደቡብ ግብፅ፤ በስሜን በኩል ደቡብ ዐረቢያ እና ስሜናዊ ሱማሌ፣ በኢትዮጵያ፣በዐረቢያ፣በግሪክ በሳባ ጥንታዊ ቋንቋ በተጻፈ ዜና መዋዕሎች ሰዎቸ እያለ የሚጠራቸዉ መሀዛ፣ሀራ፣ደመወ፣ፈልሀ፣ዕራይ፣ሀሌን፣ ምጤን፣ ዳኬን ወዘተ የተባሉትን የጦር ድርጅቶችን ሲሆን አባቶቸ የሚላቸዉ አርስ፣አሰተር፣ብሄር፣ምድር፣ የሰማዩ አምላክ፣ክርስቶስ አብ ወልደ መንፈስ ቅዱስ ወዘተ የሚባሉ የዉጭ እና የአገር ዉስጥ አማልዕክት እንደነበሩት እና የአትዮጵያ የአጼ መንግሥት የአራቱ አጎራባች የስሜን ምስራቅ አፍሪካ ክፈለ አህጉር፣ የዐባይ ሸለቆ፣የቀይባህር እና የዐረቢያ አገሮች ሉዓላዊ የበላይ ሀይል እና ሥርዓት እንደነበረ፣ ከኢትዮጵያ የአጼ መንግሥታት ግዛቶች ሂሚያር፣ረይዳ፣ሀበሻ፣ሳባን እና ሳልሄን የመነግሥቱ አምስት የዐረቢያ ግዛቶች እንደሆኑ፤ የአጼ ኢዛና እና የአጼ ካሌብ የድንጋይ ላይ ጽሁፎች እንደሚታወቀዉ በቤጃ እና በሚሮዋ ህዝቦች እና አገሮች ላይ እየሰፋ የመጡ የኢትዮጵያ የአጼ መንግሥት የቀይባህር እና የዐባይ ሸለቆ ግዛቶች ናቸዉ፡፡ ንጉስ ካሌብ ኑቢያን፣ሚወርን፣ናፓታ እና ደቡብ ዐረቢያን የአሁኑ የመንን ከ525 እስከ 576 ዓ.ም ገዝተዋል፡፡ (ፓንክኸርት ገጽ 52)፡፡
የግብፁ ተስፋፊ መሪ መሀመድ አሊ ከ1805 እስከ1849ዓ.ም በኦቶማንቱርክ የበላይነት ሱዳንን ተቆጣጥሮ ከ1820 እስከ 1822ዓ.ም በስሜን ኑቢያን በምዕራብ ዳርፉርን በመሀል ኮረዶፋን በደቡብ በጉሳ አለቆች ይተዳደሩ የነበሩትን በአጠቃላይ በአረብ ቋንቋ ብለድአል ሱዳን ብሎ ጠራዉ፡፡ትርጉሙም የጥቁሮች አገር ማለት ነዉ፡፡ ከሰሃራ በታች የአለዉ አካባቢ አንዳንዱ ካርታ ሱዳን ሲል፤ አንዳንዱ ደግሞ ኢትዮጵያ የሚል ነዉ፡፡በኢዛና ጊዜ ከሰሀራ በታች ያሉ አገሮች በአንድ ተጠቃለዉ ነበር፡፡ጣሊያን፣ እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ቅኝ ግዛትን ለማሰፋፋት ኢተዮጵያን እየኮረኮሙ ወሰዷት እንጂ ትልቅ አገር ነበረች፡፡የኢትዮጵያ ግዛት የተረጋገጠበት የጀበና ቅርጽ ግዛታዊ ክልል የያዘችዉ በአምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት ነዉ፡፡
የኢትዮጵያ መልካምድራዊ አቀማመጥ የየዘመኑ ሀያላን ሀይሎች መራኮቻ መድረክ መሆን
እኤአ በ1869ዓ.ም ሜዲትራኒያንን ከቀይ ባህር ጋር የአገናኝዉን የስዊዝ ቦይን(ስዊዝካናል) የከፈቱት ወይም የገነቡት የምዕራብ ምስራቁን ዓለም የባህር ላይ መስመር ከመቆጣጠር ዘሎ የአዉሮፓ፣ የእስያ፣ የአፍሪካ፣ የአሜሪካ እና የአዉስትራሊያ አህጉሮችን በንግድ በማያያዝ የምዕራቡን ዓለም የበላይነት ለማስፈን እንደሆነ ታሪኩ ያሳያል፡፡
የስዊዝ ቦይ መከፈት ቀይባህር፣ የኤደን የባህር ሰላጤእና የህንድ ዉቅያኖስ ከአሜሪካ እና ከአዉሮፓ ወደ እስያ ለሚተላለፉ መርከቦች አቋራጭ መስመር ሁኖ ከማገልገሉም በላይ አፍሪካን ዙሮ ይደረግ የነበረዉን የተራዘመዉን ጉዞ በማሳጠር የዓለምን የንግድ እና መሰል ግንኙነቶችን ቀላል እና ቀልጣፋ እንዲሆን ማድረጉ ጥርጥር የለዉም፡፡
የነዳጂ ዘይት ገዢ የሆኑ አገሮች ከአምራችዎቹ ከዐረቡ ዓለም ወደ ምስራቅ ቻይና እና ጃፓን ወደ ምእራብ አዉሮፓ አገሮች አሜሪካ ከፍተኛ መጠን የአለዉ ሸቀጥ ጭምር የሚቀባበሉበት የባህር ጎዳና በመሆኑ፤ ኢትዮጵያ በዚህ የባህር በር መተላለፊያ በራፍ ላይ የምትገኝ በመሆኗ ለተለያዩ ተጽዕኖዎች ተጋላጭ አድርጓታል፡፡
እንግሊዝ የሲዊዝ ቦይን መቆጣጠር ማለት ፤ቀይ ባህርን መቆጣጠር ማለት ነዉ፡፡ ቀይባህርን መቆጣጠር ደግሞ መካከለኛዉ ምስራቅን መቆጣጠርነዉ፡፡መካከለኛዉ ምስራቅን መቆጣጠር ማለት ደግሞ፣ የአፍሪካ ቀንድን እና እሩቅ ምስራቅን መቆጣጠር ነዉ ከሚል ድምዳሜ ደረሰች፡፡በዚህ ስሌትም መሰረት እንግሊዝ ፣ፈረነሳይ እና ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር ከቀጥተኛ እስከ እጅ አዙር ወረራ አደረጉ፡፡
ምዕራባዊያን የቀይ ባህርን ዳርቻ ቀድሞ በንግድ መተላለፊያነት የሚታወቀዉን አካባቢ በመቆጣጠር የጥቅማቸዉ ማስጠበቂያ እንደ አደረጉ ሁሉ፤ የነዳጂ ሀብት ምንጭ የሆነዉን የመካከለኛዉን ምስራቅ በአጠቃላይም የዐረቡን ዓለም በተጽዕኖአቸዉ ሥር አደረጉ፡፡ይህ አካባቢ ደግሞ ክርስትና፣ እስልምና እና አይሁድ ሀይማኖቶች መነሻ ነዉ፡፡
ይህ ሁሉ ተደምሮ አካባቢዉን የዓለም ጂኦ ፖለቲካ አምብርት እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ቀይባህር በዓለም መልካ ምድራዊ አቀማመጥ በያዘዉ እስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ እና በከርሰ ምድር በአቀፈዉ የነዳጅ ሀብት ምክንያት በየጊዜዉ የተነሱ የዓለም ሀያላን አካባቢዉን በተጽዕኖ ሥር ለማድረግ የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል፡ ፖርቹጋሎች ፣ኦቶማንቱርኮች፣ እንግሊዞች፣ ፈረንሳይዎች፣ ጣሊያኖችእና ጀርመኖች ዘግይተዉ አሜሪካኖች የከልሉ ብቸኛ ገዥዎች ለመሆን ጥረዋል፡፡ በዚህም ምክንት አካባቢዉ በነዚህ ዘመነኛ እጅ የመግባት እና የመዉጣት ዕጣ ሲገጥመዉ ኑሮአል፡፡በተለይ በ15ኛዉ ክፍለ ዘመን ኦቶማንቱርክ መካከለኛዉ ምስራቅን፣ ደቡባዊ አዉሮፓን እና ስሜን አሜሪካን በተቆጣጠረበት ወቅት፤ ምፅዋን፣በጎስን እና ሀልሀል የተባሉትን የባህረ ነጋሽ/ኤርትራ/ወረዳዎች በቱርክ እና በግብፆች እጅ ወድቀዉ እንደነበር ይታወቃል፡፡
በ19ኛዉ ክፍለ ዘመን የአዉሮፓ ቅኝ ገዥዎች አፍሪካን በተቀራመቱበት ዘመን እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ እና ጣሊያን በቀይባህር ምእራባዊ ዳርቻ አግራቸዉን ተከለዉ ነበር፡፡ እንግሊዝ ግብጽን እና ሱዳንን በመያዝ በርበራን ቋሚ ሠፈር አደረገች፡፡ፈረንሳይ ጅቡቲን በመያዝ ወደቡን እና የአካባቢዉን መሬት የግሏ አደረገች፡፡ጣሊያን ደቡባዊ ሱማሌን በመያዝ ሞቃዲሾን ተቆጣጠረች፡፡ በተለይ ከ1861 እስከ1874ዓ.ም በአለዉ ጊዜ ጣሊያን ከአሰብ ስሜናዊ አቅጣጫ ወደ ምጽዋ ግዛቷን በማስፋት አስተዳደሯን በማጠንከር ቆየች፡፡
በ1877 በእንግሊዝ መንግስት ተባባሪነት ምፅዋን ያዘች ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በተለይ ከ1881ዓ.ም በኋላ ጣሊያን የበህረ ነጋሽን ምድር/ኤርትራን/ ኤርትራ የሚል ስም ሰጥታ ለ50 ዓመታት ገዛች፡፡በ2ኛዉ የዓለም ጦርነት ጓደኞቿ ጀርመን እና ጣሊያን ሲሸነፉ እንግሊዝ በጣሊያን እግር ተተክታ ኤርትራን ለአሥር ዓመታት ገዛች፡፡ ይህም በጦርነት ኢትዮጵያን ለማጥፋት የአደረጉት የርብርብ ጥፋት ሲከሽፍባቸዉ በባንድነት ሲያገለግ ሏቸዉ በነበሩ የልጅ ልጆቻቸዉ(ሻቢያ እና ወያኔ) በፈጠሩት የማጥፋት ዘመቻ ኤርትራን ገንጥለዉ ኢትዮጵያን ወደብ አለባ እንድትሆን አደረጉ፡፡በ19ኛዉ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ እስከ አሁን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ በማያቋርጥ ሁኔታ ቀይ-ባህርን እና አካባቢዉን በተጽኖአቸዉ ሥር ለማዋል በሚሹ ኃይሎች ጥቃት እየተሰነዘረባት ነዉ፡፡በ19ኛዉ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ እስከአሁን የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ታሪክ በማቋርጥ ሁኔታ በዉጭ አደጋ የታጀበ ነዉ፡፡
በ1869ዓ.ም እኤአ የስዊዝ ቦይ በመከፈቱ የግብፅ ከዲቭ እስማኤል በቀይባህር ጠረፍ እና አካባቢዉ ላይ ሥልጣኑን ለማስፋፋት እቅድ አወጣ፡፡ጥቃቱንም የቱርክ ይዞታ በሆኑት የስሜን ምስራቅ አፍሪካ ቀበሌዎች ላይ አነጣጠረ፡፡ በ1868ዓ.ም እኤአመጋቢት 20 ቀን ምፅዋ ከቱርክ ይዞታነት ወደ ከዲቭ እስማኤል እጅ ተዛወረች፡ ግብፅም ከሱማሌ ጠረፍ እስከ ጋርዱፍ የአለዉን አካባቢ ተቆጣጠረ፡፤ኢትዮጵያንም ለመዉረር ወሰነ፡፡ በእንግሊዙ የጦር መኮነን መሪ ወርልድ ሙዚንገር የጦር መሪነት በ1872 ከከረን እስከ ቢሌን የአሉትን የኢትዮጵያ ቀበሌዎች ያዘ፡፡የግዛት ወሰኑንም ለማስፋፋት የኢትዮጵያን ሰሜናዊ እና ምስራቃዊ ግዛት በቁጥጥሩ ሥር ለማዋል በ1875ዓ.ም በሦስት አቅጣጫ ጦሩን አሰለፈ፡፡
ይኸዉም
1ኛ በራዉፍፐሽ አዛዥነት ሀረርን ይዞ የግብፅ መንግስት አካል በማድረግ ህዝቡን አሰለመ፡፡
2ኛ በሙንዚንገር አዛዥነት ከታጁራ ወደ መሀል ኢትዮጵያ ለመሄድ የተንቀሳቅሰዉን የወረራ ኃይል የአዉሳ ሱልጣናዊ መረፊ ሂዳር ወር በ1875ዓ.ም አዉሳ በርሃ ላይ በመግጠም ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር ድባቅ መትቶ የወረራዉን ዕቅድ አከሸፈ፡፡
3ኛ በሻምበል አረንፒሩን እና አርመናዊ አራኪል በ1875 ዓ›ም ጉንዴት ላይ በአጼ ዮሀንስ እና በራስ አሉላ አባነጋ ጦር ድል በመመታት የወራሪዉን ቅስም ሰብረዉ ሸኙት፡፡ግብፅ ይህ የተደጋገመ ሽንፈት ያስከተለባትን ዉርደት ለማካከስ ሙሉይ ሃሰን ፓሽ በጀርመናዊ የጦር መኮነን የሚመራ የሰለጠን ከ60 ሺህ በላይ ጦር ይዞ በ1876ዓ.ም ጉራይ ላይ በአጼዮሀንስ ከሚመራዉ ጦር ጋር ገጠመ፡፡ በሙሉይ ሀሰን ፓሻ የሚመራዉ የግብፅ ጦር እንደ አለፉት ሁሉ ድል ተመታ፡፡
በዚህ ጦርነት የተማረከዉ ሙላይ ሀሰን ፓሻ ከአጼ ዮሀንስ ፊት ቀርቦ የድሉን ቀን ለማስታወስ ከክንዱ ላይ ሁለት መስቀል ተወቀረለት ፡፡በነዚህ ተከታታይ ድሎች ተስፋ የቆረጠችዉ ግብፅ በተሸናፊነት ስሜት ዉስጥ ወድቃ ንጉሠ ነገሥቱን እርቅ ጠየቀች ፡፡እርቅም ሆነ፡፡ በእርቁም ሙላይ፣ ሙንዚንገር እና ሌሎችም እስረኞች በስምምነቱ መሰረት ከእስር ተለቀቁ፡፡
ከ1860ዉቹ ጀምሮ የአዉሮፓ ካፒተሊዝም ወደ ኢምፔሪያሊዝም ለመሸጋገር እንቅስቃሴ የጀመረበት እና አፍሪካን ለመቀራመት እቅድ የአወጣበት ጊዜ እንደነበር ይታወሳል፡፡ በዚህ ዘመን እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ኃያላን ከሚባሉት አገሮች ዉስጥ የሚመደቡ ነበሩ፡፡ ቀድሞ ከ10ኛዉ እስከ 15ኛዉ ክፍለ ዘመን ቱርክ፣ አስፔን እና ፖርቹጋል ኃያላን አገሮች እንደነበሩ ይታወቃል፡፡ከግዙፉ የቄሳር ግዛቷ ዉስጥ ግብፅ አንዷ ነበረች፡፡ ከ1794 እስከ 1797ዓ.ም ናፖሊዮን በጁ አድርጓት ነበር ፡፡ግብፅ ገዥወቿ ሹ መት የሚያገኙት በቱርክ ባለሥልጣኖች ሁኖ የሚፀድቀዉ አስታንቡል ዉስጥ ነበር፡፡ ከ 1797 እስከ 1840ዓ.ም የግብፁ ባሻ የነበረዉ መሀመድ አሊ የናፖሊወንን ጦር ከግብፅ በማባረሩ የዘመናዊተ ግብፅ መስራች ሆነ፡፡ መሀመድ አሊ ግብፅን ከፈረንሳይ ነፃ ከአወጣ በኋላ የዐባይን ወንዝ ለመያዝ በመተማ በኩል ተደጋጋሚ የወረራ ሙከራ ቢያደርግም ሳይሳካለት ቀርቷል፡፡ መሀመድ አሊ ሲሞት 4ኛ ልጁ የሆነዉ ሰይድ በአባቱ ቦታ ተተካ፡፡
ሰይድ መሀመድ ስልጣን እንደያዘ የበላይ ጌታዉን የቱርክን ሡልጣን አስፈቅዶ የስዊዝን ቦይ በፈረንሳይ መሃንዲስ ዴሊ ሳንስ አማካይነት አስቆፈረ፡፡ ግብፅ በስዊዝ ቦይ መከፈት በተቋቋመዉ ማህበር ዉስጥ አክሲዎኖች መሸጥ ጀመረች፡፡ ሆኖም ሰይድ መሀመድ ስዊዝ ቦዩ አገልግሎት ከመሰጠቱ በፊት ሞተ፡፡ በ1855ዓ.ም ከዲቭ እስማኤል የግብፅ መሪ ሆነ፡፡ከዲቭ ስልጣን እንደያዘ የቱርክን ሱልጣን ጋብዞ በማስጎብኘት ከዲቭ ባሻ ወይም ጌታዉ የሚል የመዕረግ ስም ተሰጠዉ፡፡በሌላ በኩል ግብፅ ዓመታዊ ግብር ሳያቋርጥ ለቱርክ እንድትከፍል ሆኖ፣ ግን ነጻ መንግሥት እንደሆነች ተበሰረዉ፡፡በ 1886ዓ.ም ቦዩ በኩባንያ መልክ ተቋቁሞ ስራዉን ጀመረ፡፡ ከዲቭ በአክሲዮን ሽያጭ ከቀረጥ በሚገኘዉ ገቢ የጦር ሀይሉን አጠናከረ፡፡በዚህ ዘመን አስፔን እና ፖረቹጋል እየተዳከሙ በአንጻሩ እንግሊዝ እና ፈረነሳይ እየገነኑ በመሄድ ላይ ነበሩ፡፡ በመሆኑም እንግሊዝ ከግብጽ ጋር ወዳጅነት መሰረተች፡፡
ከዲቭ እስማኤል የግብፅን ኢኮኖሚ ለማንሰራራት እና ለማሰፋፋት ዓልሞ ሲንሳ ዋናዉ ዓላማዉ ዓባይን ለመቆጣጠር ኢትዮጵያን መቆጣጠር በሚል እሳቤ ቀደም ሲል ቱርክ ይዛዉ የቆየችዉን ምጽዋን እና ሱአኪምን በ1863 ዓ›ም በፊርማ ከቱርክ ተረክበ፡፡ ሱዳንን ይዞታዉ በማድረግ ኡጋንዳን አና የኒያንዛን በህር ዘልቆ በርካታ የአፍሪካ አገሮችን ለመያዝ ቻለ፡፡
ለዚህ ስኬት ከጀርባ እንግሊዝ እና ፈረንሳይ አይዞህ ባይነት ነበረበት፡፡በቀይ ባህር እና በህንድ ዉቅያኖስ የአሉ ወደቦችን የሚቆጣጠረዉ በቱርክ የበላይነት ግብፅ ነበረች፡፡ በግብፅ መሳሪያነት የቱርክ መስፋፋት የአሳሰባቸዉ ፈረንሳይ እና እንግሊዝ በግብጽ ላይ መዶለት ጀመሩ፡፡ በወቅቱ ጀርመን እሩሲያ እና ኦስትሪያ ስጋት አልነበሩም፡፡ ጣሊያንም ከፊል በኦስትሪያ ከፊል በፈረንሳይ ተወስዳ ስለነበር በ1853 ዓ.ም ነበር እንደ አንድ መንግሥት የቆመችዉ፡፡በሌላ በኩል በወቅቱ ፈረንሳይ እና እንግሊዝ ተፎካካሪ ነበሩ፡፡
በ1884ዓ.ም እኤአ የስዊዝን ቦይ መከፈት ተከትሎ 12 አዉሮፓ አገሮች አሜሪካ እና ሶብየትህብረት በአጠቃላይ 14 አገሩች አፍሪካን ለመቀራመት የስምምነት ዉሳኔ አሳለፉ፡፡የሥምምነት ዉሳኔዉም በመካከላቸዉ የእርስበርስ ግጭት እነዳይፈጠር በወረራዉ ጊዜአንድ ኃይል ቀድሞ የያዘዉን አገር ለሌላዉ እንዲያሳዉቅ የሚል ነበር፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት የአፍሪካን ካርታ ዳግም ለመሳል ሲጥሩ፤ኢትዮጵያ የቅርጫዉ ድረሻ እንድትሆን ተስማሙ፡፡
በዚህ ስምምነት መሰረት ጣሊያን በ1996 ዓ.ም እኤአ ኢትዮጵያን በእጁ ለማድረግ ወረራ ከፈተ፡፡ ባህር አቋርጦ የመጣዉን የኢጣሊያን ቅኝ ገዥ ኃይል ይደረጋል ቀረቶ ይታሰባል በማይባልበት መልኩ በእምየ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ የተመራዉ የኢትዮጵያ ሰራዊት የኢጣሊያንን ጦር በአንደቀን ጀምበር በአድዋላይ ድባቅ መትቶ በመመለስ ፤ኢትዮጵያ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ቀንዲል እና ዓርማ ሆና እንድትቀጥል የአደረገዉን ድል አስመዘገበች፡፡ዓለምንም አስደመመች፡፡ ነግሦ የነበረዉን የነጭ የበላይነት ስሜት ገፈፈች፡፡ነጭ በጥቁሮች መደፈር ብቻ ሳይሆን ማሸነፍ እንደሚቻል በተግባር አሳየች፡፡ይህም ቅኝ ገዢ ኃይሎች በአፍሪካ እና በእስያ ላይ የነበራቸዉን ፖሊሲ በእክሮ እነዲመለከቱ እና እንዲለዉጡ ግድ አላቸዉ፡፡
ግብጽ ከአፍሪካ አገሮች በብዙዎች ቅኝ የተገዛች ኃያላን አገሮች በእርሷ መረማመጃነት ገብተዉ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ለሚሹ አገሮች አብሪ ተባባሪ እና መሪ በመሆን ያገለገለች ብቸኛዋ አፍሪካዊ አገር ነች፡፡ግብፅ በታላቋ አለክሳንደሪያ ከተወረረችበት ጀምሮ እስከ 1957ዓ.ም ነፃ እስከ ወጣችበትጊዜ ድረስ ከግሪክ ወደ ሮም ከዚያም በአረቦች ተወስዳ በቱርክ እና በጀርመን በመጨረሻም በእንግሊዝ የተገዛች የቅኝ ገዢ ኃይሎች የቅኝ አገዛዝ መርህ መለማመጃ የሆነች አገር እንደሆነች ታሪኳ ያስረዳል፡፡
ከመሰረቱም ግብፅ ወደ እስያ እና ወደ ሜዲትራኒያን በህር መሸጋገሪያ ድልድይ እንጂ እንደ ሉዐላዊ አገር አልነበረችም ፡፡ ከፈርኦኖች ዘመን አንስቶ እስከ 1952 እስከ ወደቀዉ ንጉስ ፋሩቅ ድረስ ማንም ግብፃዊ ግብጽን አልገዛም ገዢዎቹ መሳፍንቶች የዉጭ ዜጋ ነበሩ፡፡በግብፅ ምድር ጥሩጥሩ ነገሮች ሁሉ ለሌሎች ነበሩ፡፡
ግብፅ ከ1841 እስከ 1914ዓ.ም የኦቶማን እምፓየር እራስ ገዝ ክፍለ ሀገር ነበረች በ1882ዓ.ም እንግሊዝ ግብፅን በይፋ ወረረች፡፡በዚያን ወቅትከግብፅ ጋር መጋጨት ማለት ከሁለት ወይም ከዚያን በላይ የአዉሮፓን ኃያላን አገሮች በቀጥታ መጋጨት ማለት ነዉ፡፡ በ1875ዓ.ም በነጠላ ወይም በጥምረት በቅኝ ግዛት ኃይሎች አይዞሽ ባይነት ከደቡብ ሱዳን አልፎ የአሉትን ግዛቶች ኢትዮጵያን ጨምሮ ለመዉረር ዘመቻ ከፈተች፡፡ በዚህም የኤደንን ባህረ ሰላጤ የዘይላን እና በርበራ ወደቦችን በመቆጣጠር ወደ መሀል አገር በመግባት ሃረርን ያዘች፡፡ ወደ ስሜን የሀደዉ ጦር ሂዳር 18 ቀን 1875 ዓ.ም ጉንዴት ላይ በ1876 ዓ.ም ጉራዕይ ላይ በ1885 ዓ.ም ኩፊት ላይ በ1880ዓ.ም ዓ.ም ሰንቲት ላይ በ1887 ዓ.ም ዓ.ም ስሩጢ እና ዶጋሌ ላይ በ 1899ዓ.ም አይላት ላይ በተከታታየ በኢትዮጵያ አርበኞች ድለ ተመቱ፡፡ በ1571ዓ.ም ቱርኮችድሆኖ ላይ በ1824፣26፣29፣30እና32ዓ.ም ግብፆችን ባህረነጋሽ ላይ በ1867/68ዓ.ም/ግብፅን ጉንዳጉንዴት እና ጉራዕይ ላይ በ1879/80/ዓ.ም ጣሊያንን ሰዓጢ እና ኩንፊት ላይ በ1877+ዓ.ም ድረቡሾችን ኩንፊት ላይ በ1896ዓ.ም ጣሊያንን አምባልጌ መቀሌ አደዋ ላይ ከ1928 እስከ 1933ዓ.ም ጣሊያንን በኢትዮጵያ ምደር ላይ መክታ አሳፍራ የመለሰች የነፃ እና የኩሩ ህዝብ አገር ኢትዮጵያ ናት፡፡
የአዉሮፓዊያን ቅን ገዥዎች ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር በተደጋጋሚ በእጅ አዙርም ሆነ በቀጥታ በጦርነት ሞክረዉ መሸነፋቸዉን ሲያረጋግጡ፤ ኢትዮጵያ ላለመጠቃት የሚያስችላት ምክንያት ምን እነደሆነ ለማስ ጠናት ሁሉም ኃያላን አገሮች ልዩልዩ አጥኝዎችን በንግድ፣ በዲፕሎማሲ፣ በጉብኝት፣ በወንጌል ስብከት እና በአሳሽነት ወዘተ በየጊዜዉ ሰላይዎችን አሰርገዉ በማሰገባት፤ የኢትዮጵያን ምንነት እና ማንነት በዝርዝር አጠኑ፡፡፡፡በ1520ዓ.ም ፖርቹጋሎች በወታደራዊ እርዳታ ስም ገብተዉ ፀረ-ኢትዮጵያ አንድነት፣የእስልምና እና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖቶች ተገዳዳሪ የሆነ ሃይማኖት ችግኝ ተከሉ፡፡በ1635ዓ.ም በአጼ ፋሲል ኖሊንግ የተባለ ፕሮቴሰታንት የዮሃንስን ወንጌል ወደ አማርኛ የተረጎመ፤ በ1829ዓ.ም ሳሙኤል ጉባት እና ኩግለር የተባሉ ሚሺነሪዎች ከትግራይ ገዥዎች ከነደጃዝማች ሳባጋዲስ እና ዉቤ ሀይለማርያም ወዘተ ጋር በመገናኘት መወዳጀት ሞከሩ፡፡ በ1833ዓ.ም ቻርለስ ኢዘንበርግ የተባለ የኩግለር ተከታይ ኢተዮጵያ ገባ፡፡ በ1833ዓ.ም ዮሃን ክራፍ የተባለ የቨትስበርግ ተወላጅ ጀርመናዊ ፕሮቴስታንት እና ሰላይ ወደ ሽዋ በመገባት ከንጉስ ሳህለ ስላሴ ጋር ተወዳጀ፡፡ የዮሀን ክራፍ ትኩረት ከሽዋ በስተደቡብ ያለዉን በስፋት ጋሎች (ኦሮሞዎች) የሰፈሩባቸዉን አካባቢዎች ለጀርመን ለመካከለኛዉ አፍሪካ ቅኝ ግዛት መረማመጃ ምቹ መስፈንጠሪያ ቦታ ማመቻቸት ላይ ነዉ፡፡በጥናቱም ጋሎች አንድ ዓይነት ቋንቋ የማይናገሩ፤አንድ ዓይነት ሥነ ልቦና የሌላቸዉ፤ ተመሳሳይ ታሪክ ያልገነቡ ወዘተ መሆኑን ተረዳ፡፡ይህ ደግሞ ጀርመን ለምትመኘዉ የመካከለኛዉ አፍሪካ መቆጣጠሪያ መነሻ መሬት ሊጠቅም የማይችል መሆኑን ተገነዘበ፡፡ ለጀርመን የሚጠቅመዉ ጋሎች (ኦሮሞዎች) አንድ ዓይነት ቋንቋ፣ተመሳሳይ ታሪክ እና ስነልቦና እንዲሁም የጋራ የኛ የሚሉት የመሬት ክልል ሲኖራቸዉ እንደሆነ አመነ፡፡የነገዱ አባሎች የፍላጎቱ ተጋሪዎች እንዲሆኑ ጋላ የሚለዉን ስም የሰጣቸዉ ዐረቦች እና ሀበሾች ናቸዉ፡፡በመሆኑም ቋንቋቸዉን ኦሮሚኛ፣ ነገዳቸዉን ኦሮሞ ፣ ግዛታቸዉን ኦሮሚያ ማለት እንዳለባቸዉ ለጀርመን መንግሥት በመጽሀፍ ጽፎ አሳወቀ፡፡ለዚህ ዓላማ ማስፋፊያ የሚሆን ጊንቢ ዉስጥ የፕሮቴስታንት ሃይማኖት ማስፋፊያ አቋቁሞ ሄደ፡፡በዚህም መነሻነት የኦሮሞ የተማረ ትዉልድ ይህን እራሱን ኦሮሞን እና ኢትዮጵያን የሚያጠፋ የጀርመን ዓላማ ትክክልነዉ ብለዉ ከሜጫ ቱሉማ አስከ ኦነግ የአሉ ድርጅቶች ከሰፊዉ ማንነታቸዉ ወጥተዉ፤ ልክ እንደ ቅኝ ገዢ ኃይሎች ዐማራን ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን እና ዘዉዳዊ ሥርዓቱን በጠላት ነት ፈርጀዉ ኢትዮጵያ አሁን ለምትገኝበት ምስቅልቅል ሁኔታ ዳርገዋታል፡፡
የተለያዩ ሰላይዎች እና ፀረ-ኢትዮጵያ ግለሰቦች ዐማራን በማጥፋት ኢትዮጵያን ማጥፋት አንደሚቻል ለተገንጣይዎች የአቀበሏቸዉ የጥፋት ምክረ ሀሳቦች፡-
ሮማን ፐርቻስካ ኢትዮጵያ የባሩደ በርሚል በሚል ርዕስ በ 1936 ዓ.ም እኤአ በጻፈዉ መጽሀፉ ሌሎች ነገዶች ዐማራን በጠላትነት ፈርጀዉ እንዲያጠቁት የሚያነሳሳ ፀረ,ዐማራ እና የኢትዮጵያ አንድነት የሆነ ሀሳብ አትሞ አሰራጨ ፡፡በዚሁ ዘመን ጣሊያን የአደዋን ዉርደት እና ሽንፈት ለመበቀል ከ40
ዓመት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ዝግጅት በኋላ በኢትዮጵያ ላይ ወረራ መክፈቷ ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያም እንደ አደዋዉ ሁሉ ጦርነቱን በአንድ ቀን ባትቋጨዉም የወራሪዉን የኢጣሊያን ጦር በአምስት ዓመታት የመረረ የአርበኝነት ትግል የጣሊያን ፋሽስትን ቀጥቅጦ በማስወጣት በባርነት ለሚማቅቁ የአፍሪካ ሕዝቦች ዳግም የተስፋ ብርሀንነቷን እና የነጻነት ቀንዲልነቷን አሳይታለች፡፡
ሮማን ፐርቻስካ በዚህ መጥሀፉ ኢትዮጵያ የሚሄዱ አዉሮፓዊያን ከሌላዉ ዓለም ሕዝብ የሚያገኙትን ክብር እና አዛዥነት አጡ ፡፡ኢትዮጵያ የምትባል አገር ዐማራ የሚባል ሕዝብ ከጃፓን ጋር ግንባር ፈጠሮ በዚህ በመታገዝ ከነጭ ዘር ጋር የሞት ሽረት ትግሉን ጀምሯል፡፡ይህም ወደ አዋሳኝ አገሮችም ተሸጋግሮአል፡፡በአፍሪካ ዉስጥ የሚገኙ ሁሉም የቅኝ ገዥ አገሮች በአዉሮፓዊያን ላይ የሚሰነዘረዉን ፀረ ቅኝ ገዥ ጦርት ለመከላከል፤ ቅድሚያ ዐማራ ከተባለዉ ነገድ ላይ ሌሎች ነገዶች በጠላት ነት እንዲዘምቱበት ማድረግ፤ ቅደሚያ ሊሰጠዉ የሚገባ ተግባር እንደሆነ ሰበከ፡፡ ነገሩ ይበልጥ ጠንክሮ ሥር ከሰደደ የአዉሮፓ ሥልጣኔ ሊያስገኝ የሚችለዉን ጠቀሜታ ከመጥፋቱ በፊት፤ በዐማራዉ ላይ አስፈላጊዉ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚገባ አስተማረ፡፡በኢትዮጵያ በአሉት አዉሮፓዉያን ላይ የሚደርስባቸዉን የገንዘብም ሆነ የፖለቲካ በደል እና ግፍ በጀኔባ ለሚገኘዉ የዓለም መንግስታት ማህበር ቢሮ በማመልከቴ በጥር ወር 1934 ዓ.ም ከአገር እንዲወጣ መደረጉን በመጥቀስ ሀቁን ለመደበቅ ሞክሯል፡፡ሀቁ ግን ሮማን ፐርቻስካ ከአገር የተባረረዉ የሞሶሎኒ ሰላይ ሁኖ በመገኘቱ ነዉ፡፡
ሮማን ፐርቻስካ ኢትዮጵያን በቋንቋ ለመከፋፈል እንዲያመቸዉ ሕዝቡን በአራት ቋንቋዎች መደቧል፡፡ እነዚህም የአፍሮ-አስያ (የኩሽቋንቋ) ፣የሴም ቋንቋዎች፣ የኦሞቲክ ቋንቋዎች፣ የዐባይ ሠሃራዊ ቋንቋዎች በማለት ፅሁፉን ለዓለም አሰራጨ፡፡ በዚሀ መሰረት ጣሊያን ኢትዮጵያ ላይ ለአምስት ዓመታት በአርበኝነት ትግል እየተናጠ በቆየባቸዉ ዓመታት ዉስጥ ኢትዮጵያ የሚለዉን ነባር ስም ለዉጦ የምስራቅ አፍሪካ የጣሊያን አስተዳደር በሚል ተካ፡፡ዉስጣዊ አስተዳደሩንም በሚከተለዉ መልኩ ከፋፈለ፡፡
1ኛ ትግራይ ትግርኝ (ኤርትራንና ትግሬን አንድ በማድረግ)ዋና ከተማ አስመራ፣ ቋንቋ ትግርኛ፤
2ኛ አማራ (ጎንደር፣ ጎጃም፣ወሎ እና ከፊል ሽዋን አንድ በማድረግ) ዋና ከተማ ጎንደር ቋንቋ አማርኛ፤
3ኛ ጋላ- ሲዳሞ (ወለጋን፣ኢሉባቡርን፣ከፋን፣ሲዳሞና ጋሞጎፋን አንድ በማድረግ)ዋና ከተማ ጂማ ቋንቋ ኦሮሚኛ፤
4ኛ ሀረርጌ (አሩሲ እናሀረርጌን አንድ በማድረግ) ዋና ከተማ ሀረር ቋንቋ ዐረብኛ፤
5ኛ ሱማሊያ (ሶማሊያን እና ኦጋዴን አንድ በማድረግ) ዋና ከተማ ሞቃድሾ ቋንቋ ሱማሌኛ ፤
6ኛ ሽዋ ( አዲስ አበባ እና ማዕከላዊ ሽዋን አንድ በማድረግ) ዋና ከተማ አዲስ አበባ ቋንቋ ዐማርኛ፤ በማለትከፋፈል፡፡
ፕሮፌሰር ሰብሰኪ የኢትዮጵያ ታሪክ በፋሽስት ኢጣሊያን ወረራ ወቅት በሚል ዕርስ በጻፈዉ ጽሁፍ የኢጣሊያን ዋና ግብ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች በአንድላይ እንዳይኖሩ መበታተን እንደሆነ አስረድቷል፡፡ ለዚህ ግብ ተፈፃሚነት ቀናዉ መንገድ ሆኖ የአገኘዉ ዐማራን በሌሎች ብሄረሰቦች ማስጠላት የሚል ነዉ ፡፡ ጀምስ ብሩስ የአባይ ወንዝ መነሻ ወደሆነችዉ ኢትዮጵያ የተደረገ ጉዞ በሚለዉ ጽሁፉ ኢትዮጵያዊያንን አጥላልቶ እና ኮንኖ ጽፏል፡ ከዲቭ እስማኤል ኢጥዮጵያ ዘመናዊ አስተዳደር መስርታ፣ ዘመናዊ ጦር ገንብታ እና ከምዕራቡ ሀገር ወዳጅ ከሆነች፤ የግብፅ ህልዉና
አደጋ ዉስጥ እንደሚገባ ስጋቱን ገልፆአል፡፡የግብፅን ህልዉና ዘላቂና አስተማማኝ ለማድረግ፣ ከሚከተሉት አንዱን ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝቧል፡፡ አንደኛ የኢትዮጵያን ሕዝብ ወደ እስልምና ሃይማኖት መለወጥ ካልተቻለ፣ አገሪቱ ወደ እድገት ማህበራዊ መረጋጋት እና የጠነከረ አንድነት እንዳት ገነባ ፤ዘወትር የእርስ በርስ ፍጥጫ ተወጥራ እንድትያዝ ፣ዐማራ በተባለዉ ነገድ(ብሄር) ላይ የማነሳሳት ዘመቻ በተከታታይ የሚካሄድበትን መንገድ በስራ ላይ ማዋል፤ ለግብፅ ህልዉ አስተማማኝ እንደሚሆን እምነቱን እና ፍልጎቱ ገልፆአል፡፡ በዚህ ዓላማም መሰረት ግብፅ በተደጋጋሚ ኢትዮጵያን ወሮ እስላም ለማድረግ ሙከራዋን የኢትዮጵያ ሕዝብ በተባበረ ክንዱ ማክሸፉ እዉቅ ነዉ፡፡ግብፅ በቀጥታ ወረራ ኢትዮጵያን መቆጣጠር እና የማስለም ፍላጎቷ አለመሳካቱን ከተገነዘበች በኋላ፤ የአደረገችዉ፤ በእጅ አዙር ጦርነት የሕዝቡን አንድነት ማላላት፤ እድገቷን ማጓተት እና ሰላሟን ማወክ ወደሚለዉ ተሸጋገረች፡፡ በዚህም ሻቢያን በተከታታይም በስሜን በደቡብ የአገሪቱ ክፍሎች ተገንጣይ ቡድኖችን በማደራጀት እና በማስታጠቅ እንዲሁም ዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ በመስጠት የኢትዮጵያን ሰላም እና አንድነት እየተፈታተኑት እንዳሉ በተከታታይ እና በግልፅ እየታዩ ነዉ፡፡
ረቻርደ ኮፕላንድ የተባለ አሜሪካዊ የተማሪ ሰላይ ለኢሳይያስ እረዳት በመሆን ኤርትራን እንድትገነጠል የሚስችለዉን መንገድ አሳየ፡፡ኤርትራም ይኸዉና በ30 ዓመታት እልህ አሰጨራሽ በሆነ በፀረ ዐማራ እና ፀረ ኢትዮጵያ ቡድኖች እረዳ ተራዳ በ1983 ዓ.ም ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠል ሆነ፡፡ መገንጠሏብቻ ሳይሆን፤ገንጣይወቹ እራሳቸዉ እስከሚገርማቸዉ ድረስ መለስዜናዊ አሰብን በግድ ዉሰዱ ብሎ ሰጥቶ አገሪቱ ዝግ መሬት እንድትሆን አድርጓል፡፡ ሩዶልፍ የተባለ ጸሀፊ በበኩሉ ዐማራ ለኢትዮጵያ የቆመ ሀይል ነዉ፡፡ ዐማራ እንዳይደራጅ ጠብቁት፡፡ የሞተ ዐማራ አይነሳም ብሎ ማመን እንጂ የተዳከመ ዐማራ አይነሳም ብሎ ማመን ቂልነት ነዉ፡፡ በማለት በዓማራዉ ላይ ያለዉን ጥላቻ እና እየመረረዉ ቢሆንም ዐማራዉ የኢትዮጵያ አስተማማኝ ኃይል እንደሆነ ፤ ዐማራዉ ከተደራጀ እና በአንድነት ከቆመ ለፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች የማይበገር እንደሆነ በመገንዘቡ ፤ እንደይደራጅ ማድረግ ልዩ ትኩረት ሊደረግበት እንደሚገባ ለተገንጣይዎች ምክሩን ሰጥቷል፡፡ ይህም ብቻ አይደለም፡፡ ዐማራ ሙቶ እየአዩት እንኳን ተመልሶ ቢደክምም እንደገና አንሰራርቶ የመነሳት ኃይል የአለዉ መሆኑን አበክሮ በፍራቻ በፅሁፉ አስፍሮአል፡፡ይህ ነዉ የዐማራዉ ትልቁ እሴቱ እና ሥነልቦናዊ ብቃቱ፡፡ የዛሬዉ የዐማራዉ ኃይል ይህ ሥነ ልቦናዉና መከራዉን አንገት ደፍቶ በማሳለፉ እራሱን አቅንቶ ጠላቱን ድባቅ የመምታት ባህል ያዳበረ እና ይህ ባህል ፈፅሞ ያልጠፋ መሆኑ ነዉ፡፡ እነዚህ ፀረዐማራ የሆኑ በማስተማር ፣በዲፕሎማሲ እና በሃይማኖት ማስፋፋት ስም ወደ አገራችን የገቡ ሰላይዎች፤ በየፈርጁ ኢትዮጵያ ልትዳከምበት እና ልትፈራርስበት የምትችልበትን መንገዶች አጥንተዉ የደረሱበት መደምደሚያ፤ለኢትዮጵያ በጦርነት ድልአድራጊነት ጥንካሬ የሚሰጡት ሦስት ጥንታዊ ዘመን ጠገብ የሆኑ ተቋሞች እንዳሉ ተረዱ እነዚህ፡- 1 የሥልጣን ምንጭ እና የአንድነት ምልክት የሆነ ዘዉዳዊ ሥርዓት፤ 2 የዘዉዳዊ ሥርዓት ዕርዮተዓለማዊ ክንድ እና የህዝቡ የእምነት መገለጫ የሆነ የኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋህዱ የክርስትና ሃይማኖት፤ 3 ለዘዉዳዊ ሥርዓት እና ለሃይማኖቱ ቀናዒ የሆነ፤የአገር አንድነት እና ነጻነት ሲደፈር፤ ሥንቁን በአህያ ዉ ዓመሉን በጉያዉ ይዞ፤ከጠላት ፊት ቀድሞ የሚጋፈጥ ተዋጊ ዐማራ የተሰኘ ነገድ መሆናቸዉን በጥናታቸዉ አረጋገጡ፡፡ እኒህ ተቋሞች በሰከነ እና ተከታታይነት በአለዉ መልኩ አንዱን ከሌላዉ በመነጠል፤ ማዳከም እና መበታተን ኢትዮጵያን የማፍረሻዉ ብቸኛዉ መንገድ እንደሆነ ደመደሙ፡፡ ይህን ዕዉን ለማድረግም በአገሪቱ ዉስጥ የሚኖሩ ነገድ እና ጎሳዎችን
በማንነታቸዉ ዙሪያ በማደራጀት ዐማራዉ ጠላታቸዉ ፣ የጨቆናቸዉ፣የበዘበዛቸዉ እና ባህል እና ቋንቋቸዉን እንዳይጠቀሙ እንደ አደረጋቸዉ አድርጎ በማቅረብ እና በማስተማር በፀረ ዐማራነት እንዲቆሙ ማድረግ የዓላማቸዉ ማስፈጸሚያ ሁነኛ መሳሪያ እንደሆነ አስተማሩ፡፡ጻፉ፡ ፡ ሰበኩ፡፡ ይህ ትምህርት እና ስብከት ተስፋፍቶ ይኸዉና ከ80 በላይ የነገድ ድርጅቶች ተፈልፍለዉ ዐማራን እና ኢትዮጵያን ለማጥፋት ሌት ከቀን እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ለዚህ ሁሉ መንገዱን ያሳየችዉ ጣሊያን ናት፡፡ጣሊያን ኢትዮጵን በ88 ነገዶች እና ጎሳዎች(ብሔር ብሔረሰቦች) ሸነሸነች እነሱም የሚከተሉ ናቸዉ፡፡
የአባቹ ኦሮሞ፣ የአፋር ህዝብ፣ የዳዉሮ ህዝብ፣ የዲዚ ህዝብ፣ የአገዉ ህዝብ፣ የዶርዜ ህዝብ፣ የአማራ ህዝብ፣ የጋብረ ህዝብ፣ የአንዋክ ህዝብ፣ የጋዳ ህዝብ፣ የአርባሮ ህዝብ፣ የጋሞ ህዝብ፣ የአርጎባ ህዝብ የጌዲዮ ህዝብ የአርመኒያን በኢትዮጵያ፣ የጎፋ ህዝብ፣የዐዊ ህዝብ፣ የግሪክ በኢትዮጵያ፣ የባና ህዝብ፣ የጉምዝ ህዝብ፣ የባስኬቶ ህዝብ፣ የጉራጌ ህዝብ፣ የቤኒአመር ህዝብ፣ ሐድያ ህዝብ፣ የበርታ ህዝብ፣ የሀድያ ሲዊታናት ህዝብ፣ የቤተ አብርሀም ህዝብ፣ የሀላባ ህዝብ፣ የቻራ ህዝብ፣ የሀማር ህዝብ፣ የችቦ ህዝብ፣ የሀረሬ ህዝብ፣ የቻይና ህዝብ በኢተዮጵያ፣ የሀርካ ህዝብ፣ የዳላንች ህዝብ፣ የኤሮ ህዝብ፣ የዳንታ ህዝብ፣ የኢጣሊያን ህዝብ፣ የጃማይካ በኢትዮጵያ፣ የሽታ ህዝብ፣ የጂቡቲ ህዝብ፣ የሲዳማ ህዝብ፣ የካፊቾ ህዝብ፣ የስልጠየ ህዝብ፣ የከምባታ ህዝብ፣ የማድሂባን፣ የከረዮ ኦሮሞ ህዝብ፣ የሶማሌ፣ የኪችፓ ህዝብ፣ የቶማል፣ የኮንሶ ህዝብ፣ የሱርማ ህዝብ ፣ የኩር ህዝብ፣ የቲግራያን፣ የኩናማ ህዝብ፣ የቲርማ ህዝብ፣ የኩዋማ ህዝብ፣ የጻማል ህዝብ፣ የከዌጉ ህዝብ፣ የቱሉማ ኦሮሞ ህዝብ፣ የማሌ ህዝብ፣ የወላይታ ህዝብ፣ የሚጫ ኦሮሞ ህዝብ፣ የወርጅ ህዝብ፣ የማጃንግ ህዝብ፣ የወይጦ ህዝብ፣ የሚያ ኢትዮጵያ፣ የወሎ ኦሮሞ፣ የመካን ህዝብ፣ የየጁ ኦሮሞ ህዝብ፣ የሙርሌ ህዝብ፣ የየም ህዝብ፣ የሙርሲ ህዝብ፣ የዜየ ህዝብ የኑዌር ህዝብ፣ የናንጋቶም ህዝብ የኢሳይያስን ዱካ ተናጋሪ፣ የኦሮሞ ህዝብ፣ ያማንት ህዝብ፣ የራያ ኦሮሞ ህዝብ፣ የሬርባር ህዝብ ፣ የሳሆ ህዝብ፣ የሽቦ ህዝብ፣ የሻንቅላ ህዝብ እና የሽናሻ ህዝብ ብላ ከፋፈለች፡፡
ጣሊያን ለኮሎኒያሊዝም ጥቅም እና ጸጥታ አደገኛ ጠላት ዐማራ ነዉ፡፡ በማለት ዐማራን እና ኦርቶዶክስ ሃይማኖት እንዲጠፉ ከፍተኛ የሆነ ዘመቻ አካሂዷል፡፡በዚህም ዘመቻ ከ600 አስከ800ሺህ ዐማራ ከሚኖርበት ከሀረር፣ ከጋላ ሲዳማ ተፈናቅለዉ ወደሽዋ እንዲሰደዱ ተደርጓል፡፡ከኃላፊነት እና ከሥራ ተባረዋል፡፡ ዐማርኛ በሌሎች ክልሎች የመንግሥት ሥራ እንዳይሰራበት ተከልክሏል (ዶ/ር ላጲሶ ገጽ 69 እሰከ 70)
የኢንዱስትሪ አብዮት
የኢንዱስትሪ አብዮት በ1750ዓ.ም በብሪታኒያ መጀመሩ ይታወቃል፡፡በአብዮቱ ሁለተኛዉ ምዕራፍ ላይ አዳዲስ ፍላጎቶች ጎልተዉ መጡ፡፡ እነዚህም ፍላጎቶች (1) አፍሪካን በቅኝግዛት በመያዝ እረካሽ ጉልበት መቆጣጠር (2) ጥሬ እቃ መዝረፍ (3) ሰፈራ ማካሄድ (4) የእንበስትሜንት አማራጭ ማየት እና ሰፊ ገብያ መፍጠር ዋነኛዉ ነበሩ፡፡ እና መነሻቸዉ ሆነ፡፡ ይህን ከፍተኛ ፍላጎት ተከትሎ ዓይናቸዉን ወደ አፍሪካ ቀድመዉ የጣሉት ፖርቹጋል፣ እስፔን፣ቤልጅም፣ብርታኒያ፣ፈረንሳይ፣ ጀርመን እና ጣሊያን ሆኑ፡፡ የኢንዱስትሪ አብዮት በአሰከተለዉ በአሮጌዉ እና በአዲሱ ማህበራዊ ሥርዓቶች መካከል ማለትም፤ በሁለት ተከታታይ እና ተቃራኒ የምርት ሀይሎች እና የምርት ግንኙነቶች መካከል በሚፈጠረዉ ሥርዓታዊ ቅራኔ እና ግጭት ምክንያት በ1917 ዓ.ም በሌኒን የሚመራዉ የቮልሸቢክ ፓርቲ፤ በዛሩ ፊዉዳላዊ የሩስያ አገዛዝ ላይ፣የሶሻሊስት ዐቢዮት በማካሄድ ከምእራቡ ዓለም የተለየ አዲስ የምርት ግንኙነት ለዉጥ ተካሄደ፡፡ በ1917 በሩሲያ የተካሄደዉ ዐብዮት ለዉጥ እስከ 1986 ለ70 ዓመታት ያህል የዓለምን አንደ ሦስተኛ( ሢሦዉን) በመያዝ ዓለማችን ቡለት ተፃራሪ ርዕዮቶች ዓለሞች እና ሥርዓቶች ማለትም ካፒታሊዝም እና ሶሻሊዝም ከፋፍሎ ጥይት የአልጮኸበት የቀዝቃዛዉ ጦርነት ዘመን ሁኖ እንደአለፈ አይዘነጋም፡፡
ከሁሉም በላይ ከ1920 ዎቹ እስከ 1940 ዎቹ የቡርዧዉ ፋሽስቶች እና ከበርቴዎች የካፒታሊዝም ሥርዓትን ከወዛደራዊ አብዮት እና ከኮሚኒዝም ሥርዓት እናድናለን በሚል በከፈቱት ጦር ነት፤ በተለይ በጀርመን እና በጣሊያን መንግሥታዊ አምባ ገነኖች መሪነት የተካሄደዉ ፀረ ወዛደር እና ፀረ ሶሻሊዝም ጦርነት የፖለቲካ ፍልስፍና ሁኖ ተከሰተ፡፡ በአደዋ ላይ ኢትዮጵያ ባስመዘገበችዉ ድል የተቋጩት እና የተነገበገቡት አንግሊዝ፣ ፈረንሳይ ወዘተ በአጋርነት በኢጣሊያን መሪነት በ1928 ዓ.ም ኢትዮጵያን ስትወር የትግራይ ትግርኝ የባንዳ ጦር አሰልፎ የአርበኝነት ተግሉን አጠንክሮ በነበረዉ የሽዋ ክ/ሀገርን ሀዝብ በራያ ባንዳወች አስወረረዉ የራያ ባንዳ የኢትዮጵን ዘር ለማጥፋት በሚል የወንድ ልጅን የዘር ብልት እየሸለተ እንዲጨረስ አደረገ፡፡ጣሊያን ከኋላ በከባድ መሳሪያ በአዉሮፕላን እየታገዘ ከኤርትራ እና ከትግራይ በቅንጅት ሰልጥኖ የተሰለፈዉ ከሀዲ ጦር አሰልፎ አርበኞችን ደበደበ፡፡እኛ ኢትዮጵያዊያን እና የትግራይ ትግርኝ ህዝብ አብረን በታሪክ የመጣነዉ እስከ 1881 ዓ.ም ድረስ ብቻ ነዉ፡፡ተወደደም ተጠላም ሕዝቡ እና ዘረኛዉ የባንዳ መደብ አብረዉ ነዉ የመጡ የሚጋሩትን ስነ ልቦና አብረዉ ነዉ የፈጠሩ ስለሆነም በታሪክ ሚዛን ላይ የትግራይ ትግርኝን ሕዝብ እና ሊመራዉ የመጣ የዘረኛ የባንዳን መደብ ለይቶ ማስቀመጥ ያስቸግራል፡፡
ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የትርራይ ትግርኝ ታሪክ ለኢጣሊያ ለፀረ ኢትዮጵያ መስፋፋት ደሙን ሲያፈስ የነበረ ሕዝብ ታሪክ ነዉ፡፡የእስከ ዛሬዉ ታሬካችን የታሪክ አቀራረብ በይሉኝታ የተደረተ እንደነበር ሊታወቅ ይገባል፡፡ ባንዳ ከላቲን ቋንቋ የመጣ ነዉ፡፡ጣሊያን ወደ ደጋዉ ኤርትራ እንደ ደረሰች በእቅፍ አበባ የተቀበሏት የትግራይ ትግርኝ የዉራጃ ገዥዎች ነበሩ፡፡ እስከ አሁንም የነዚህ ልጆች እና ዘሮች ናቸዉ በፀረ ኢትዮጵያ ዓርማ ስር ለመቆም የተሰለፉት ለወደፊቱም ወራሽ መደባቸዉ በማስተላለፍ ላይ ይገኛሉ፡፡(ተስፋየ መኮነን ትወልድ እናቅርሱ ገጽ 28 ) ጣሊያን ከወጣ በኋላ ይሰጥ የነበረዉ ዘመናዊ ትምህርት 95 ከመቶዉ ዕርዮተ ዓለም 5 ከመቶዉ ሙያ ነበር፡፡ ምእራባዊያን ዕርዮተ ዓላማቸዉን በኢትዮጵያ ያዘራጩት በብዙ መንገድ ነዉ፡፡ ከነዚህም ጥቂቶቹ በዩነቨርሲቲዉ፣ በመጽሀፍት፣ በፊልም ፣በፕሮቴስታንት ሀይማኖት እና በተለያዩ ተቋማት አማካይነት ኢትዮጵያ የምትደከምባቸዉን የምትፈራርስባቸዉን ዘዴዎች በረቀቀ እና ተከታታይነት በአለዉ መልኩ አስፋፍተዋል፡፡ የዚህ ፀረ ዐማራ እና ፀረ ኢትዮጵያ የሆነ ፕሮፖጋንዳ ወጥመድ ሰለባዎች ከነበሩት ዉስጥ ዋለልኝ መኮነን፣ ብርሀነ መስቀል እረዳ፣ክፍሉ ታደሰ ፣ ተስፋየ ደበሳይ፣ ኢሳይስ አፈወርቄ፣መለስ ዜናዊ ዲማ ነጎ፣ ሌንጮለታ፣ወዘተ ቀዳሚዎች ሆኑ፡፡ በ1943 ዓ.ም በኢትዮጵያ ለዘመናዊ ትምህርትየአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ መከፈቱ እና ፣የትምህርት ፖሊሲዉ እና ሥርዓተ ትምህርቱ በምዕራባዊያን ምሁራን መዘጋጀቱ እና ዩንቨርሲቲዉ በምዕራባዊያን ምሁራን እንዲያዝ መደረጉ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ለአሰፈሰፉ ኃይሎች ምቹ የዘር መዝሪያና ማምረቻ ሆነላቸዉ፡፡ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት በተለያየ ጊዜ ሰላየዎቻቸዉ የአቀረቡትን ጥናት በዘመናዊ ትምህርት ቤት በእዉቀ ት ማስፋፋት ስም በወጣቱ ትኩስ አዕምሮ ዉስጥ ሳይጠይቅ እና ሳያመዛዝን ለማስረጽ የተመቻቸ እድል አገኙ፡፡በዚህም እስበሱ ስጋን በኩበት ጠበሱ እንዲሉ፤ እንዲጠፉ የአሰቧቸዉን ተቋማት፤ ማለትም የአንድነት ምልክት እና የሥልጣኔ ምንጭ የሖነዉን ዘዉዳዊ ሥርዓት፤የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትእና የዐማራዉን ነገድ ለማጥፋት የኢትዮጵያ ተማሪዎች እንቅስቃሴ የሚባለዉ መሰረቱ፡፡ የተቃዉሞ ቡድን የጥፋታቸዉ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ሆነላቸዉ፡፡ ዘር ተኮር የሆነ እንቅስቃሴ የተጀመረዉ፤ ለዉጥ ምን እንደ ሆነ፤ከለዉጡምን እንደሚጠበቅ እናለዉጡ ሊያስከትላቸዉ የሚችሉትን ዙሪያገብ ቀዉሶች ምን
ለሆኑ እንደሚችሉ ፍንጭ የለላቸዉ፤ በአንድ ጀሮ ሰምተዉ በአንድ ቃል የነበረዉን ሥርዓት የአወግዙ በነበሩ ተማሪዎች ነበር፡፡ ተማሪን ከተማሪ በዘር መለየት የተጀመረዉ ዩንቨርሲቲዉስጥ እንደ ነበር እና የኢትዮጵያ ችግር መነሻዉ በ1ኛ እና በ2ኛ ደረጃ ትምህርትቤቶች ሳይሆን በዩንቨርሲቲዉ ሊሂቃን ተብየዎች መካከል መሆኑን ማወቅ ለመፍትሄዉ አፈላለግ እንደሚረዳ ፕሮፌሰር መራራ ጉዲና በአንድ ስራዉ አረጋግጧል፡፡በመቀጠልም በዋለልኝ ስብከት በዩንቨርሲቲዉ ተማሪዎች ስብሰባ ላይ በአማርኛ መናገር ክልክል ፣የተከለከለ እንደነበር በግልፅ ይታወቃል፡፡
በ1966ዓ.ም ግርማቸዉ የሚብል የዩንቨርሲቲዉ የፖለቲካ ሳይንስ ተማሪ የሆነዉ የማህበራዊ ሳይንስ ተወካይ ለመሆን ለዉድድር ቀርቦ በአማርኛ የተዋጣለት ንግግር አደረገ፡፡ በንግግሩ ተማሪዎች ተመስጠዉ በከፍተኛ ጭብጨባ አድናቆታቸዉን ገለጹለት፡፡ ተናጋሪዉ ዐማራ በመሆኑ እና ንግግሩንም በዐማርኛ ማድረጉ የአበሳጨዉ ትግሬዉ (ኤርትራዊዉ) የስብሰባዉ ሰብሳቢ መለስ ተክሌ በክፍተኛ ንዴት እና ግንፍልነት ተነስቶ፤ይህ የደብተራ ልጅ በታጋይዎች ደም በተገነባዉ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ መድረክ ላይ ቁሞ የሚተፋዉን ሰምተሰችሁ እንዴት ታጨበጭባላችሁ ፤ ብሎ በመጮህ በተሰብሳቢዎች ላይ ዛተ፡፡
መለስ ተክሌም በዚህብቻ ሳይወሰን ግርማቸዉ በዚህ ንግግሩ ፈተና እንዲወድቅ የራሱን የበየትሥራ እንደሰራ ይነገራል፡፡ ግርማቸዉ ግን ወደቆ አልቀረም፡፡ የዐማርኛ ችሎታዉ የተዋጣለት ስለነበር ትግላችን የተሰኘዉ የዩንቨርሲቲዉ ተማሪዎች መፅሄት የዐመርኛ ክፍል አዘጋጅ ሁኖ አገልግሏል፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ዐማርኛ ወደ ዩኘቨርሲቲዉ መግቢያ መሆን ከሚያስፈልጉት መስፈርቶች አንዱ እንዳይሆን መታገዱን ፕሮፌሰር መራራጉዲና በመፅሀፋቸዉ ጠቅሰዋል፡፡
ከዚህላይ ልብ ልንለዉ የሚገባ ግርማቸዉ በዐማርኛ ጥሩ ንግግር አደረጎ ስሜት ስቦ በማስጨብጨቡ አብረዉት በሚማሩት ተማሪዎች መብቱ ከመገፈፉ አልፎ ፈተና እንዲወድቅ መደረጉ፤ በዩንቨርሲቲዉ ዉስጥ ዐማርኛ ቋንቋ እና ዐማራ የቱን ያህል ተማሪዉ እንዲጠየፋቸዉ ይደረግ እንደነበር ጉልህ ማሳያ ነዉ፡፡
በ1958ዓ.ም ከተሰጠዉ ትምህርት በመነሳት በዩንቨርሲቲዉ ተማሪዎች መካከል በሚደረግ የግጥም ዉድድር ከተማሪዎቹ አንዱ የሆነዉ ኢብሳ ጉተማ ማነዉ ኢተዮጵያዊ በሚል ዕርስ ግጥም አቀረበ፡፡ የግጥሙ መሰረታዊ ጭብጥም አንዱን ነገድ ጨቋኝ ሌሎችን ተጨቋኝ አድርጎ ማሳየት ነበር፡፡ ግቡም የኢትዮጵያ ነገድ እና ጎሳዎች በማንነት ዙሪያ ተደራጅተዉ አንድነታቸዉን እንዲንዱ፤አዲስ ማንነት እነዲላበሱ የሚያነሳሳ ነበር፡፡ በመሆኑም ግጥሙ ኢትዮጵያን እና ዐማራን የሚያወግዝ በመሆኑ የዓመቱ ምርጥ ግጥም ተብሎ ገጣሚዉ እንዲሞገስ እና እንዲ ሸለም ተደረገ፡፡ከጥቂት ወራት በኋላ ኃይለማርያም ጎሹ ከኢብሳ ጉተማ በተቃራኒ ኢትዮጵያነት ከግላዊ፣ ጎሳዊ እና አካባቢያዊ እምነት የዘለለ ምጡቅ እና እረቂቅ ማንነት እንደሆነ የሚያመለክት ጽሁፍ አቀረበ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በዩንቨርሲተዉ ህትመቶች ዉስጥ ኢትዮጵያዊነት ላይ የአተከሩ ጽሁፎች ብቅብቅ ማለት ሲጀምሩ በተማሪዎች እንቅስቃሴ ዉስጥ አክራሪ አመለካከት እና አሰላለፍን አስከተለ፡፡
የተመሪዎች በነገድ የመከፋፈል መዘዝ ተካሮ በ1959 ዓ.ም ከቃላት ወደ አካላዊ ግጭት አመራ፡፡ በመሆኑም በዚህ ዓመት የዐማራ ተማሪዎች እና የተግሬ ተማሪዎች በዩንቨርሲቲዉ የትምህርት ፋካሊቲ በላቮራቶሪዉ ክፍል ዉስጥ ተደባደቡ፡፡ምዕራባዊ ይዘቱ የአመዘነዉ ዘመናዊ ትምህርት በተማረዉ ዉስጥ ከሚጭረዉ የምክንያታዊነት፣ የመሻሻል፣ የእኩልነት፣ የብቃት ወዘተ እሴቶች እዉን ሁነዉ የማየት ፍልጎት ከተጨባጩ ሀገራዊ ህይወት እዉነታ የተቀየረ መሆኑ እራሱን የቻለ ሥነ ልቦናዊ ግፊት ነበር፡፡ ይህን ኢትዮጵያን ብሎም ዐማራን ለማጥፋት የመጀመሪያዉ ባለዉለታቸዉ ደቀመዝሙር ዋለልኝ መኮነን ነዉ፡፡ዋለልኝ መኮነን ሂዳር 10 ቀን በ1961 ዓ.ም
ታገል በሚል ረዕስ በዩንቨርሲቲዉ መጽሄት ባሳተመዉ ጽሁፍ ጨቋኙ የዐማራ ብሄር ነዉ የዐማሮች ኢትዮጵያ፣ኢትዮጵያዊ ለመሆን በአማራ ስም መታወቂያ መያዝ ነዉ፡፡ ከአልሆነ ዜግነትህ አይከበርም፡፡ ኢተዮጵያ የብሄረሰቦች እስር ቤት ናት አሳሪዉም ዐማራ ነዉ በማለት ቀሰቀሰ፡፡
ዋለልኝ በ1962 ዓ.ም የብሄር ጥያቄ በኢትዮጵያ በሚል እርስ የአሰራጨዉ የሮማን ፐርቻስካን ጽሁፍ በቀጥታ ገልብጦ ነበር የጽሁፉ ፍሬ መለዕክትም የተማሪዎች እንቅስቃሴ ምዕራባዊያን የወሰኑባቸዉን ነባረ፣ታሪካዊ እና በህላዊ ተቋሞች የሆኑትን ዘዉዳዊ ሥርዓቱን የኢትዮጵያኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን እና የዐማራዉን ነገድ እንዲያጠፉ ቆርጦ እንዲነሳ ማድረግ ነበር፡፡አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች መጀመሪያ ስራቸዉ በብሔር መቧደን ነዉ፡፡ በዚህ የአፈጻጸም ስልት ዘዉዳዊ ሥርዓቱን አጥፍተዉ ኦርቶዶክስ ሃይማኖትን እና የአማራዉን ነገድ ለማጥፋት ነበር፡፡ የሚገርመዉ የዐማራተማሪዎች ሌሎች በብሄራቸዉ ተደራጅተዉ ዐማራዉን ለማጥፋት ሌት ከቀን ሲታተሩ፤ዐማራዉ በሬ ከአራጁ ጋር ይዉላል እንዲሉ የአንዱ ወይም የሌላዉ ደጋፊ ወይም ተቃዋሚ ከመሆን ዉጭ ለዐማራዉ ህልዉና ለመቆም ምልክት አላሳዩም ነበር፡፡በወቅቱ የነበሩ የተማሪ መሪዎች በጠባብ ስብሰባዎች ዉሳኔ እየአሳለፉ አብዛኛዉን ተማሪ ማንቀሳቀስ፤ በተማሪዎች ንቅናቄ ሽፋን በብሄር መደራጀት ዩንቨርሲቲዉ ተማሪዎች ከሚያስፈጽማቸዉ ተግባረት የመጀመሪያዉ እንዲሆን አድርገዉ ያዙ፡፡ የኦሮሞ ተማሪዎች መጨና ቱሉማ የልማት መህበር በሚል ሽፋን ኦነግን ለመመስረት ኦሮሞዎችን በማሰባሰብ፣ በማንቃት እና በማደራጀት ኦነግ በ1966ዓ.ም ሲመሰረት ዮሃንስ ነጎ/ዲማ/ሊቀመንበር ሞሄ ምክትል ሊቀመንበር በመሆን ተመርጠዉ ኦሮሞን ለመገንጠል መንቀሳቀሳቸዉ አሁን እየተሰራ የአለዉ ኢትዮጵያን የማጥፋት ሰራ ጉልህ ማስረጃ ነዉ፡፡ በዚህ ዙሪያ ተሰብስበዉ ከነበሩት የኦሮሞ ተማሪዎች መካከል አቦ ምትኩ፣ አየለ ዘዉገ፣መሰለ ደባ፣ዮሃንስ ባንቲ/ገላሳ ዲልቦ/ እና ፍስሀ አዱኛ ይገኙበታል፡፡
የትግራይ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች መህበር /ትዩተማ/ በ1958 ዓ.ም ሲመሰረት መስራቾቹ ብረሀነ መስቀል እረዳ፣አበበ ተሰማ፣ሃይሌ አጽብሀ፣ዮሀንስ ስብሀቱ፣መለስ ተክሌ፣ዘሩ ክሽን፣ ግደይ ገብረዋህድ፣ ወልደስላሴ ነጋ፣ገብረኪዳን ደስታ፣ዮሀንስ ተክለ ሃይማኖት፣ ጥላሁን ግዛዉ፣ሀጎስ ገብረየስ፣ አረጋዊ በርሄ፣ገብረመስቀል ሃይሉ የተባሉት የትግሬ ተማሪዎች የንጉሠ ነገሥቱን አስተዳደር ለመጣል የትግራይን ተማሪ አደራጁ፡፡ አደራጅተዉም ዓላማቸዉ እና ገባቸዉም የትግራይ ሕዝብ አንደኛ እና ቀንደኛ ጠላት ዐማራ መሆኑን እና ዐማራ ካልጠፋ የትግራይ ሕዝብ ከርሀብ ከድህነት መላቀቅ ስለማይችል፤ ዐማራን ጨርሶ ለማጥፋት የትጥቅ ትግል ከገጠር ወደ ከተማ ማካሄድ እንደአለባቸዉ፣ የትግራይን ወጣት ከገጠር እስከ ከተማ አስተማሩ፡፡ በዚህም መሰረት በጥርወር 1967 ዓ.ም 10 አባላት ለስልጠና ወደሕዝባዊ ግንባር ኤርትራ በየካቲትወር ደግሞ 1967 ዓ.ም አስራ አንድ አባላት የትጥቅ ትግል ለመጀመር ደደቢት ወረዱ፡፡የትግሬ ወያኔዎች በረሀ ለመግብት ምክንያት የአደረጉት ሥልጣናችን በሽዋ ምኒልክ በመቀማታችን ለርሀብ እና ለችግር ዳርጎናል፡፡ ዐማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ነዉ ፡፡የሚል ነዉ፡፡
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴየሥልጣን ዘመን ግንቦት 2 ቀን 1933 ዓ.ም የሾሟቸዉ ሚኒሰቴሮች
ደጃዝማች መኮነን እንዳልካቸዉ የአገር ግዛት ሚኒስቴር
አቶ/ደጀማች/መኮነን ደስታ የትምህርት ሚኒስቴር
አቶ ወልደ ገወርጊስ ወልደ ዮሀንስ የጽህፈት ቤት ሚኒስቴር
አቶ/ብላታ ጌታ/ ሎሬንስ የዉጭጉዳይ
አቶ ገብረእግዚአብሄር ደስታ የንግድ እናኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
ብላታ አየለ ገብሬ የፍርድ ሚኒስቴር
አቶ በላቸዉ ያዴታ የፖስታ እና ቴሌግራም ሚኒስቴር ናቸዉ፡፡
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የሥልጣን ዘመን ሌሎች ጠቅላይ ግዛቶች በእንደራሴ ሲተዳደሩ ትግሬ ጠቅላይ ግዛት የሚተዳደረዉ በአጼ ዮሃንስ የልጅ ልጆች በገዥነት ነበር፡፡ይህም የሆነዉ በልማቱ፣ በበጀቱ እና በአጠቃላይ በኢኮኖሚዉ ከንጉሡ ትእዛዝ ዉጭ ለመስራት እንዲያስችል በራስ ገዥነት የሚተዳደር ነበር፡፡ ወያኔዎች በጥቅሉ ከዐማራዉ በተናጠል ደግሞ የሽዋን ዐማራ በአዉራ ጠላትነት የፈረጁ በመሆናቸዉ፤ ይህን ለማለሳለስ ንጉሰ ነገስቱ ልጃቸዉን ልዕልት ዘነበወርቅ ኃይለሥላሴን ለደጃዝማች ኃይለሥላሴ ጉግሳ፣ የልጅ ልጃቸዉን ልዕልት ይዳ ግዛዉን ለራስ መንገሻ ሥዩም በመዳር፤ ሰላም እና አንድነት እንዲፈጠር ጥረዋል፡፡ ሆኖም ደጃዥማች ኃይለሥላሴ ጉግሳ በ1928 ዓ.ም ጣሊያን ኤርትራን ሲወር ሰላሳ ሺህ ጦሩን እንደያዘ ለወራሪዉ ጣሊያን እጁን በመስጠት የመጀመሪያዉ ከሀዲ ሁኖ ኢትዮጵያን ከጣሊያን ጎን ሁኖ በአጋርነት ወግቷል፡፡ በማከታተልም ሁሉም የአጼ ዮሀንሰ የወንድም ልጆች እራስ ሥዩም መንገሻ እና ልጃቸዉ መንገሻ ሥዩም ለጣሊያን በማደር አገር እና ሕዝብ ወግተዋል፡፡ የባንዳ ልጆች የሆኑት የት ሕነግ(ሕወሓት) አባሎች እና አመራሮችበተመሳሳይ ሁኔታ ኢትዮጵያን ወግተዋል፡፡አገር ክደዋል ኤርትራን አሰገንጥለዋል፡፡ አገሪቱን ያለወደብ እንደትቀር አድርገዋል፡፡ ከ50 ዓመታት በላይ የተገነባዉን የመከላከያ የፖሊስ እና የደህንነት አባሎችን ገድለዋል፣በትነዋል፣ተቋሞቸን አፍርሰዋል፡፡ አገሪቱን በቋንቋ ሸንሽነዉ ሕዝብን ከሕዝብ በማጣላት፣ በማጋደል፣ በማሳደድ፣ አገሪቱን ገድለዋል፣ ሰላምእና ደህነነት አሳጥተዋል፡፡
በጥቅሉ የትግራይ ወያኔዎች አያቶቻቸዉ እና ወገኖቻቸዉ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ለተሰለፉት ወራሪዎች ሁሉ በባዳነት ያገለግሉ ስለነበር፤ ተወልደዉ ሲያድጉ በእምድጃ ዙሪያ ሲተረክላቸዉ የነበረዉ የእግሊዝ፣ የጣሊን፣የገበፅ ፕሮፖጋንዳ እና በዐማራ ላይ የከረረ ጥላቻ እንዲይዙ የማድረግ ነበር፡፡ለልጆቻቸዉ የአስተማሯቸዉ ለኢትዮጵያ በሰላም፣በነፃነት ለመኖር የተደረገዉን ጦርነት የአካሄደዉ የዘዉድ መንግስት፣ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ የክርስትና ሐይማኖት እና የዐማራዉ ነገድ ብቻ እንደፈጸመዉ በዚህም አባቶቻቸዉ እና ዘራቸዉ እንደአለቀ ከወራሪዎች የአገኙት የነበረዉ ዘላቂ ጥቅም እንደቀረባቸዉ፣የትግራይን ሥልጣን እንደተቀሙ፤የዉጭወራሪዎች መግቢያ በራቸዉ በትግራይ በኩል ስለሆነ ፤ባይከለከሉ የነሱ ዘር እድሜ ልካቸዉን ተጠቃሚ ይሆኑ እንደነበር፤ዐማራዉ ወራሪን ለመከላከል በሚያደርጉ ጦርነት ንብረታቸዉ እንደአለቀ፤ ችግር፣እርሀብ፣ድርቅ እንደተፈጠረ ፤የአድዋ ጦርነት በምሳሌ እየጠቀሱ አስተማሯቸዉ፡፡ከዚህ ሁሉ ለመዳን ብቸኛዉ አማራጭ የዘዉድ ሥርዓት፣ የክርስትና ሀይማኖትነ እና ዐማራን ማጥፋት እንደሆነ እና ለዚህ የትግራይ ትዉልድ በነቂስ ተደራጅቶ ለዚህ ግብ እንዲንቀሳቀስ ነገሩ፡፡አስተማሩ፡፡ የህን በተመለከተ በብሥራት አብርሃ የተጻፈዉን ከአገር በስተጀርባ የተሰኘዉን መጽሀፍ ማንበብ አራስን በመረጃ ሙሉዕ ለማድረግ ይጠቅማል፡፡
የትግራይን የባንዳዎች ታሪክ በዝርዝር ለማወቅ የሐበሻ ጀብዱ የተባለዉን መጽሃፍ አንብቦ የትግሬን ባንዳዎች ከሌላዉ ሕዝብ መለየት በእጅጉ ይረዳል፡፡የባንዳ ወላጆቻቸዉን ትምህርት በመከተል ነዉ፡፡ የባንዳ ልጆች በዩንቨርሲቲዉ ዉስጥ የወላጆቻቸዉን ትምህርት እነመለስ ዜናዊ በጠባብ ስብሰባቸዉ ተወያይተዉ በመወሰን ዉሳኔአቸዉን ሰፊዉን ተማሪ በፈለጉት ጊዜ ሰብስበዉ በማጸደቅ እየሰሩ ቤተመንግስት የገቡት፡፡
ትሕነግ (ሕወሓት) ዐማራዉን ለማጥፋት ግብ አድርገዉ ከአስቀመጧቸዉ ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸዉ፡፡ 1 ኢትዮጵያን ተቆጣጥሮ የትግሬ ከበርቴዎችን መፍጠር፡፡ 2 በትግራይ ከበርቴዎች ትግራይ ዉስጥ በብዛት ፋብሪካዎችን ማቋቋም፡፡ 3 ዐማራዉን ማደኽየት፣ በንግድ ፣በትምሕርት፣በማህበራዊ ጥቅም አፍኖ እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ፡፡
4 ዐማራዉን በነገድ እና በቦታ ከፋፍሎ እንዳይስማማ ማድረግ፡፡
5 ዐማራዉን ጨርሶ ለማጥፋት የትግራይን ሰፊ መንግስት መፈጠር፤ ለአፈጻጸም እንዲመች ዐማራዉን ከሌሎች ነገዶች ጋር ማጣላት፤በተለይ ዐማራ እናኦሮሞ አንድነት እንዳይፈጥሩ በተለያየ ሥልት የማጣላቱ ሥራ ሳይቋረጥ በርትቶ መስራት እንዳለባቸዉ ተማምነዉ ተግባራዊ ለማድረግ ዓለሙ፡፡ የዓለሙትንሁሉ በስኬት ለመፈጸማቸዉ ማረጋገጫቸዉን እንዲህ ሲሉ ነግረዉናል፡፡ 1 ዐማራን እና የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይን አንኮትኩተነዋል፡፡ገድለን ቀብረነዋል፡፡ሥብሀት ነጋ 2 አባቶቻችሁን ገድለን ቀብረናቸዋል፡፡እናንተንም ገድለን እንቀብራቸኋለን፡፡ሳሞራ የኑስ 3 ወገቡን ተመቶ የነበረዉ ዐማራ አንገቱን ቀና እያደረገ ነዉ፡፡ዐማራዎችን በሏቸዉ፡፡ታምራት ላይኔ 4 በአንበሳ ባንክ ምስረታ ጉባኤ ባደረገዉ ንግግር ገድለን የቀበርነዉን ዐማራ አታንሱብን፡፡ሳሞራ የኑስ በማለት ዐማራዉን በእቅድ የጨረሱት መሆኑን በሙሉ ልብ እና በኩራት አረጋግጠዋል፡፡
የኢህአፓ መስራች ባለሥልጣን እነብርሃነ መስቀል እረዳ ወዘተ ነበሩ፡፡ብርሀነ መስቀል እረዳ የብሔረሰቦች እስር ቤት ናት እያለ እስከ መገንጠል ይጽፍ ነበር፡፡ከዉጭ እንደ ተመለሰም በሻቢያ ለአንድ ዓመት ታግቶ ኤርትራ በኢትዮጵያ ቅኝ ተገዝታለች ብሎ በማመን ለሚመራዉ ኢህአፓ/ኢህአሰ/አሳምኖ ትግሉን እንዲቀጥል የተደረገዉ በኢሳኢያስ አፈወርቄ ነበር፡፡ የኢህአፓ መሪዎች ትግሬዎች ስለነበሩ ህወሀት እና ኢህአፓ በትቅምት ወር 1968ዓ.ም የአንድነት ግንኙነት መስርተዉ ፤ በ1970ዓ.ም ሚያዚያ ላይ አከተመ፡፡ ምክንያቱም ወያኔ የካቲት 18እና24 ቀን 1970 ዓ.ም ኢድህን ከአጠቃ በኋላ መጋቢት 10 ቀን 1970 ዓ.ም የወያኔ 73ኛ እና 30ኛ ኃይል በአንድ ላይ ነበለት ወረዳ መሪቶ ከሚባል መንደር ደፍጦ የኢህአፓን 74ኛ ኃይል ደምስሶ፤ በመገስገስ እምብር ላይ ስንገድላይ ቀጥሎም ፉግ ላይ መጋቢት 19 ቀን1970 ዓ.ም ኢህአፓን ደመሰሱ፡፡ የኢህአፓ መሪዎች 600 የሚሆኑ ጀብሀ ወደ ሚቆጣጠረዉ ተሸግረዉ አመለጡ፡፡በኢህአፓ ላይ ይህ ሁሉ ችግር የተፈጠረዉ መሪዎቹ ከወያኔ እና ከሻቢያ ጋር የመሰሪነት ግንኙነት በመኖሩ ነዉ ፡፡ ለዚህም መረጃ የሚሆነዉ የሀወሃት ኃይል እና የኢህአሰ ሀይል በከፍተኛ ትንቅንቅ በሶቢያ ተኩስ የከፈተዉን የህወሀትን ኃይል ለአንድ ጊዜ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለመደምሰስ የኢህአሰ ሀይል ለመክበብ በጥድፊያ ላይ እያለ የወያኔ ባለስልጣናት የአሉበት እና በኢህአፓ አጥቂነት የሚደመሰሱ መሆናቸዉን ከወያኔዎች በአለዉ ዉስጣዊ ግንኙነት የተረዱት የኢህአሰ (የኢህአፓ) አመራር የመተንፈሻ፣ የማፈግፈጊያ፣ የወንድ በር፣ ስጧቸዉ የሚል ተእዛዝ ለሀይላቸዉ ተሰጥቶ ተከቦ ለመጥፋት ተዘጋጅቶ የነበረዉ የወያኔ መሪዎች በኢህአሰ /ኢህአፓ/ መሪዎች ቸርነት ከመደምሰስ ድነዉ ለቤተመንግስት ሥልጣን መብቃታቸዉ ነዉ፡፡
በ16ኛዉ ምዕተ ዓመት የኦሮሞ ዘር ሀረግ ከ1520 እስከ 1620 ዘመን
ኦሮሞዎች በኢትዮጵያ ምድርእንደሰርዶ ታትተዉ እንደዋርካ የሰፉት የግራኝን ወረራ ተከትለዉ በአካሄዱት መጠነሰፊ የመሬት ወረራ ነዉ፡፡ ከመነሻቸዉ ዛሬ ኦሮሞ የሚባለዉ ነገድ ስሙ ጋላ ይባል የነበረዉ እንደሆነ ግንዛቤ መያዝ ተገቢ ነዉ፡፡ከጋላ ወደ ኦሮሞ እንዲቀየር ሐሳብ ያቀራዉ ዮሓን ክራፍ የተባለ ጀርመናዊ ሰላይ እና የጀርመን ቅኝ ግዛት ማስፋፊያ ዘዴ አፈላላጊ ሚሺነር ነዉ፡፡ በጥቅሉ ኦሮሞዎች ከሁለት ጎሳዎች ተነስተዉ በመባዛት የተለያዩ ጎሳዎች መመስረት እንደቻሉ የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ የመነሻ ጎሳዎቹ የሚከተሉት እንደሆኑ ብዙዎች ይስማማሉ፡፡እነዚህም፡-
ሀ የቦረና ጎሳ ሀረግ ይህ ጎሳ ከዚህ ቀጥሎ የሚዘረዘሩት ጎሳዎች ግንድ ወይም አባት ነዉ፡፡
ቦረና ስጲራን፣ ቦረናን እና ዳጨን ሦስት ይወልዳል፡፡
ዳጨ መጫን፣ዳጭሜን፣ኮኖን፣በቾን፣ጂሌን አምስት ይወልዳለ፡፡ ሜጫ ደአለን፣ጂዳን ሁለት የወልዳል ዳጭሜ ሰዶን፣አቦን፣ጋላን ሶስት ይወልዳል፡፡ ኮኖ ሳቅስን፣ሊቨንን ሁለት ይወልዳል፡፡ በቾ ኦሩን፣ኢሉን፣ ሁለት ይወልዳል፡፡ ጂሌ ኢላን፣አቦን፣ሌኢስን ሶስት ይወልዳል፡፡ ዳጭጨ፣ኮኖ፣በቾ እና ጅሌ በወል /በጋራ/ ቱሉማ ይባላሉ፡፡
ጂዳ ሀኮኮን፣ጉዱሩን፣ሊቦን ሶስት የወልዳል፡፡ ሀኮኮ አቦን፣ሁርን፣ሊሙን ሶስት የወልዳል፡፡
ጉዱሩ ሲርባን፣መሉልን፣ጮረንን ሶስት ይወልዳል፡፡ ሊቦ ወሊስን፣ኩታን፣አመንን ሶስትይወልዳል፡፡
ደአለ ሆቦን፣ ጭሌን ፣አቦን፣ሉባን አራት ይወልዳል፡፡ ሆቦ ኪረሞን፣አሙሩን ሁለት የወልዳል፡፡
አቦ ልየን፣ሊቃንን አቦኖንን ሶስት ይወልዳል፡፡ የጂዳ እና የደአለ ተወላጆች በወል/በጋራ/ሜጫ ይባላሉ፡፡
የቦረና የመጨረሻ ልጆችወሎ እና ሰደቻ ናቸዉ፡፡
ለ የበርቱማ ጎሳ ሀረግ በርቱማ ከረዮን፣መረዋን፣ኢቱን፣አክቹን፣ወረገጢቫን፣ሁምባን ስድስት ይወልዳል፡፡ መረዋ እናን፣ኡሩን፣አበጢን ሶስት የወልዳል፡፡
ከረዮ ሊበንን፣ወሎን፣ጆሌን አቦን፣ሳባን፣ በላአን ስድስት የወልዳል፡፡
ወሎ ወረቡኮን፣ወረጉራን፣ወሮኖኢሉን ሶስት ይወልዳል፡፡ የጋሎች አመጣጥ እና የዘር ግንድ አባ ባህርይ የብርብር/ጋሙጎፋ/ መነኩሴ በግዕዝ ጽፈዉ (ፕሮፌሰር ኢኞሲዮጉይዲ ከአሳተሙት መጽሀፍ ምራፍ 149 ገጽ801) የተገኘ
1 የጆሌ ነገዶች አሁን ቱሉማ የተባሉት 2 የጃዳ ነገዶች አሁን ሮቤ የተባለት
3 የጃዳ ልጅ አሁን በደቻ ተባሉ 4 የአቦ ልጆች የስዴቻ ወገኖች/ሜጫ/ይባላሉ፡፡
5 የጋላ ነገድ በረይቱማ እናቦረን የዳጫ ልጅ ነዉ፡፡
6 ሶስቱ የወሎ ልጆች ወረቡኮ፣ወረጉራዕ፣ወረኖሌኤሉ
የተለያዩ አገር አሳሾች እና የታሪክ ተመራማሪዎች ስለ ኦሮሞ (ጋላ( መነሻነት የሚከተሉትን ብለዋል፡፡ ቻርለስ ቤክ ኦሮሞ ከባሮ ወንዝ በደቡብ ምስራቅ በኩል በመነሳት ወደ ወለጋ ገባ ይላል፡፡
የእስኮቲሸ ተወላጅ ጀምስ ብሩስ በበኩሉ ኦሮሞ(ጋላ) ሲናር ከተባለ ስፍራ ሱዳን ዉስጥ ተነስተዉ ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ ያስረዳል፡፡
ክርስቶፎር እህረት የተባለዉ በእንግሊዘኛ በጻፈዉ እርስ በገጽ 88 ላይ የኦሮሞ መነሻ ስሜን ሱማሌ አካባቢ እንደሆነ አስረድቷል፡፡
በጄስፔንሰር፣ትሬሚንግሀም፣ሩንትግሮ ፎርድ፣አንቶኒዮ እና ዲአባዴ የተባሉ ጸሃፊዎች የኦሮሞ መነሻ ከዉጭ ሀገር ነዉ ይላሉ፡፡
ኤንሬኮ ቸሩሊ እና አይኤምሌዌስ የተባሉት የኦሮሞን መናሻ ከኢትዮጵያ አርቀዉታል፡፡ ሆኖም የእነዚህ ሰዎች ማስረጃ መሰረተ ቢስ እንደሆነ በኦሮሞን ታሪክ ላይ ጥናት እና ምርምር የአደረጉ ምሁራን ይስማሙበታል፡፡አቶ ይልማ ደረሴ የኦሮሞ ነገድ ከደቡብ ኢትዮጵያ ወደ ስሜን እና ምስራቅ ጎርፈዉ ብዙዉን ደጋ አገር የዘዉ የሰፈሩ ናቸዉ፡፡
በመጀመሪያ ለመዉረር የመረጣቸዉ ጃዊ የተባሉት የባርቱማ ክፍል ጎሳዎች እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡ አባ በህሪይ አሮሞዎች በአጼዮናስ ሰገድ ዘመን ከባሌ አካባቢ ገላና የሚባለዉን ወንዝ አቋርጠዉ መጡ ይላሉ፡፡
ከ1520እስከ 1620 በአንድ ምዕተ ዓመት ዉስጥ የአዋማዊ ኦሮሞ ማኅበረሰብ አራቱ የከረዮ፣የወሎ.የቱሉማ እና የሜጫ ጎሳዎች በደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ ከቦረና ቆላማ አካባቢ በፍለሳ ስመሪት በሚልባ፣በሙዳና ፣ በኪሎሌ፣በምችሌ፣በሀርሙፋ፣በቢፎሌ፣በሮባሌ፣በቢርመጂ፣በሙሉታ እናሉባ ድርጅቶች በስምንት ዓመት የፈረቃ አመራር በምስራቅ፣በመሀል፣በስሜን እና በምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቦዎች በነባር የሙስሊም የአዋማ እና የክርሰቲያን ሕዝቦች እና መንግሥታት ላይ ያካሄዱት ትልቅ የወረራ እና የሰፈራ እንቅስቃሴ ታሪክ ነዉ፡፡የወረራዉ ሂደትም የሚከተለዉን ይመስላል፡፡
1 ከ1520 እስከ 1530 ባለዉ ዘመን የተለያዩ የኦሮሞ ጎሳዎች በሚልባ ሉባ ዘመን ከቦረና ቆላማ አካባቢ ተነስተዉ የገላን ወንዝ ተሸግረዉ በምዕራብ በኩል ወደ ጥንታዊ የባሌ እስላም አገር ደረሱ፡፡
2 ከ1530 እስከ 1538 ዓ.ም ባለዉ የሙዳ ሉባ ዘመን የዋቢን ወንዝ ተሸግረዉ የተወሰኑ ወገኖች እና ቡድኖች በባሌ አገር በነዋሪነት ሰፈሩ፡፡
ከ 1538 እስከ 1546ዓ.ም በለዉ የከሎሌ ሉባ ዘመን ባሌን አልፈዉ ወደ ስሜናዊ ሀረርጌ እና አዋሽ ሸለቆ አካባቢ ደረሱ፡፡
ከ1546 እስከ 1554ዓ.ም በቢፎሊሉባ ዘመን ከደዋሮ ወደፈጠጋር ማለትም ወደ ዛሬዋ አሩሲ የረር እና ከረዩ አካበቢ በመሰፈር የአካባቢ ነባር ህዝቦችን በገባርነት መግዛት ጀመሩ፡፡
ከ1554እስከ 1562 ዓ.ም በምችሌ ሉባ ዘመን ከፈጠጋር ተነስተዉ በአዋሽ ወንዝ እና በዝዋይ ሃይቅ ክልል ወደ ዋጅ ወደ ገበርጌ ወደ ወረባ አጎራባች አገሮች ደረሱ፡፡እነዚህ የምችሌ ኦሮሞ ሰፋሪዎች የበቁሎና የፈረስ አጠቃቀም በመማር ከጦር ድርጅት እና ሥልት አኳያ በወረራ እንቅስቃሴያቸዉ ሂደት እና ስፋት ፈጣን የወረራ ሽፋን አደረጉ፡፡ በደረሱበት አካባቢ ሁሉ በነዋሪነት መስፈር ጀመሩ ቀጥሎም ከአካባቢዉ ነባር ሕዝቦች ጋር በኢኮኖሚ በባህል የመቀላቀል ሂደት ፈጠሩ፡፡
የቦረና ኦሮሞ ጎሳዎች በሀርሙፋ ሉባ ዘመን እና አመራር ከ1562 እስከ 1570ዓ.ም በስሜኑ ደጋ ማለትም በዛሬዋ ወሎ እና ጎንደር ላይ ታላቅ ጦርነት ከፈቱ፡፡
በሮባሌ ሉባ ዘመን ከ1570 እስከ 1578ዓ.ም በስሜናዊ ሽዋ እና በምስራቃዊ ጎጃም ላይ እረጅም የጥቃት ዘመቻ አካሄዱ፡፡በዚሁ በሮባሌ ሉባ ዘመን በምስራቅ ኢትዮጵያ የኦሮሞ ወራሪዎች በሀረር አካባቢ በመቶ የሚቆጠሩ የአዳል ማለትም የሀርላ መንደሮችን ያዙ፡፡በሀረር ከተማ ላይ ከበባ አደረጉ፡፡
የአዳልን መንግሥት በሀረር እና በአዉሳ አካባቢዎች ከፍለዉ መሀሉንም አጠቃለዉ ያዙ በዚህም ታላቁ የአዳል መንግስት ወደቀ፡፡
በቢርመጂሉባ ዘመን እና አመራር ከ1578 እስከ 1581 ዓ.ም በቢርመጂሉባ ዘመን እና አመራርበስሜናዊ መዕራብ ኢትዮጵያ ወደ ደንቢያ በመሀል ምዕራብ ደግሞ ወደዳሞት እና ጋፋት አካባቢዎች ደረሱ፡፡
በመጨረሻም በሙለታ ሉባ ዘመን ከ1586 እስከ1594 ዓ.ም ኦሮሞዎች በታላቅ ዝግጅት እና ግፊት በሽዋ እና በጎጃም ላይ ዘመቱ፡፡ከሙለታ ሉባ ዘመን በኋላ ግን በኦሮሞ የገዳ ስርዓት እና አመራር ላይ መሰረታዊ የለዉጥ ሁኔታ እና ሂደት መከሰት ጀመረ፡፡በዚህም አጼ ሰርፀ ድንግል ከ1563 እስከ 1597ዓ.ም በሙለታ ሉባ ዘመን የማኅበረሰቡን የወረራ ስምሪት ለተወሰነ ጊዜ ከትግራይ፣ከበጌምድር እና ከጎጃም ወደኋላ ስለመለሰዉ የኦሮሞ ማህበረሰብ በደረሱበት አካባቢ ሁሉ በኗሪነት የሰፈራ ሂደት እና ባህል ጀመሩ፡፡
በዚህ አዲስ የሰፈራ ኑሮ እና የእርሻ ሥራ ምክንያት በኦሮሞ ኅብረተሰብ ዘንድ አብዮታዊ የገዳ ሥርዓት ለዉጥ እና ተዛማጅ የሰፈራ እና የእርሻ ሥርዓት ጥንስስ ቀሰበቀስ መታየት ጀመረ፡፡
ከ1520 እስከ 1620ዓ.ም በኦሮሞ የወረራ ዘመን ስማቸዉ ተለወጦ በኦሮሚኛ የሚጠሩ አካባቢዎች
ነባር ስም የኦሮሞ ስም ነዋሪ ነገዶች ፈጠጋር አርሲ ዐማራ፣ሜያ፣አዳል፣ሀድያ
ደዋሮ ጭሮ፣ምዕራብ ሀረርጌ፣ ሀድያ ከምባታ ዐማራ ጉራጌ
እንዶጥና ጉለሌ የካ፣ፊነፊኒ፣እንጦጦ፣አደስ አበባ ሜያ ዐማራ
ግራሪያ ሰላሌ ዐማራ፣ሜያ እንደገብጣን ሜታ እና ዐማራ
ቤተ ዐማራ የጁ ዐማራ ዝሆን ዱር ጅባት እና ሜጫ ዐማራ
ወጂ ወንጂ ዐማራ ላሎቅሌ/እናሪያ/ ኢሊባቡር አንፊሎ፤ እናሪያ፡፡
ዳሞት ጎጃም፣ሊቃ እናሪያ፣ጋፋትእና ዐማራ
ቢዛሞ ወለጋ ቄለም እናሪያ፣ ጋፋት፣ አንፊሎ፣ ዐማራ፡፡ ላኮመልዛ ወሎ ዐማራእና አዳል
ቤተሳባ(ቤተሃይማኖት) ወረባቦ ዐመራ ቤተእግዚ ወረሂመኖ ዐማራ
ቤተ ጊዮርጊስ ወረኢሉ ዐማራ መካነሰላም ቃሎ ዐማራ
አንጎት ራያ ዐማራ፣ አገዉ ባሊ ባሌ ዐማራ እና ሜያ
አ(ወ) ይጃ የረርና ከረዮ ዐማራ፣ሜያ፣ሀድያ፣ከምባታ፡፡ ገሙ ጂማ፣ ዐማራ፣ጃንጀሮ
ገንዝ ጅባትና ሜጫ ዐማራ፣ሜያ፣ሀደያ፣ከምባታ፡፡ ምንጭ ሞረሽወገኔ የዐማራድርጅት ምፅዓተ ዐማራ ገጽ 14-28)
የጎንደር ዘመነ መንግስት መስራች የሆኑት አጼ ሱስንዮስ ከ1605 እስከ 1632ዓ.ም የኦሮሞ ሕዝባዊ የገዳ ስርዓትን ወደ ባላባታዊ ሥርዓት እንዲለወጥ ሂደቱን ጀመሩ፡፡
የአጼ ልብነድንግል የልጅ ልጅ የሆኑት ልኡል ሱስንዮስ ፋሲል በ1565ዓ፣ም ተወልዶ በ1580ዓ.ም በምርኮ ተወስዶ፤ የአንድ ቦኮ የተባለ የቦረና ኦሮሞ ተወላጅ በጉዲፈቻ እንዲያሣድገዉ ሆነ፡፡በዚህ የምርኮ ዘመኑ ልኡል ሱስንዮስ የኦሮሞን ቋንቋ፣ የገዳ ሥርዓትን እና፣የሉባ ጦር ዝግጅት እና ሥልትን እንዲያዉቅ እረዳዉ፡፡በ1580ዓ.ም አካባቢ በአርነት ወደ አጼ ሰርጸድንግል ቤተመንግሥት ከተመለሰ በኋላ የቤተ መንግሥቱን ወግ እና ስርዓት ተማረ፡፡ በ1597ዓ.ም አጼ ሰርጸድንግል ሲሞት አጼያዕቆብ፣ አጼዘድንግል፣ እና አጼ ሱስንዮስ ተራበተራ ሹ ም ሽር አደረጉ፡፡
በዘህ ሽኩቻ አጼ ሱስንዮስ ሸሽቶ ወደ ኦሮሚያ በመሸፈት በ1607ዓ.ም በ400የኦሮሞ ወታደሮች እርዳታ ሌሎችን ደምስሶ ሥልጣን ላይ ወጣ፡፡
ከ1605 እስከ1632 ዓ.ም አጼሱስንዮስ
1ኛ በስሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ከ1535 እስከ1543ዓ.ም አህመድ ግራኝ የመንግሥቱ ማዕከል በአደረገዉ አገር ደምቢያ ላይ አዲሱን የጎንደር መንግሥት ከ1605 እስከ 1855ዓ.ም መሰረተ፡፡
2ኛ ከሰርፀድንግል በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኦሮሞዎችን የወረራ እና የሰፈራ እንቅስቃሴ ከስሜኑ የትግራይ፣የበጌምድር፣ የላስታ፣ የደንቢያ እና የጎጃም አካባቢዎች በብረቱ ጦርነት ወደ ምስራቅ፣ወደ ደቡብ፣ወደመሀል፣ ወደ ምዕራብ አትዮጵያ ሕዝቦች እና አገሮች መለሰ፡፡
3ኛ እየሱሳዊያን በተባሉ የእስፓኝ እና የፖረቹጋል ካቶሊክ ሚሲዮናዊያን ትምህርት እና እርዳት ከዘመነ አገዉ መንግሥት በኋላ የአገሪቱነ የመጀመሪያ ቋሚ ቤተመንግሥት እና መዲና በደንቀዝ ደምቢያ ላይ መሰረተ፡፡
ከ1605 እስከ 1855ዓ፣ም ድረስ በስሜነ ምዕራብ ኢትዮጵያ በአጼሱስንዮስ የተቆረቆረዉ ጎንደር መንግሥት እና ከተማ ሥርዓት በአገሪቱ አካባቢያዊ የኦሮሞ፣የአገዉ፣የስሜን /ፈላሻ፣የጉምዝ ፣የኩናማ፣የቤጃ፣የትግሬ፣ የተግረየሳሆ፣የአፋር እና የበሌን ባህዉርታዊ ሕብረተሰብ መሰረት እና ማዕከል ሆነ፡፡በ17ኛዉ እና በ18ኛዉ ምዕተ ዓመታት በአንድ በኩል የኦሮሞ አራቱ የከረዩ፣የወሎ፣የቱሉማ እናየሜጫ ማኅበረሰቦች በየፊናቸዉ በደቡብ፣በመሃል እና በምዕራብ ኢተዮጵያ አካባቢዎች ተሰራጭተዉ በቋሚ የሰፈራ እና የእርሻ ተግባራት ሲሰማሩ፤በሌላ በኩል በዚህ አዲስ ማኅበራዊ ክስተት እና እድገት የኦሮሞ ጥንታዊ የገዳ የጋርዮሽ ዘመን እና ሥርዓት ቀስ በቀስ በባላባታዊ ስርዓት መፍረስ ጀመረ፡፡
በ1603ዓ.ም ወደኢተዮጵያ የገባዉ የእስፓኙ ካቶሊክ ሚሲዮናዊ ቄስ ፔትሮፓየዝ ከ1564 እሰከ 1622ዓ.ም የግብፁን የኦርቶዶክስ ክርስትና ትታችሁ የሮማንንካቶሊክ ክርስትና ብትቀበሉ በአገራችሁ የእስልምና፣ የፈላሻ፣የኦሮሞ እና የቱርክ ጠላቶቻችሁን የምትወጉበት ዘመነዊ የጦር መሳሪያ ከአዉሮፓ አስመጣለችኋለሁ በማለት የጎንደር መንግስታትን ያዕቆብ፣ዘድንግልእና ሱስንዮስነ ሰበከ፡፡
በዚህም ምክር አጼሱስንዮስ 1300 አመታት የነበረዉን ግብፅ አርቶዶክስ ክርስትና በአዋጅ ሰረዘ፡፡በምትኩ የሮማንን ካቶሊክ ክርስትና አፀደቀ ህዝቡ በአመፅ አሰወገደዉ የአረቶዶክስ ርስትናወደነበረዉ ቦታዎ እንዲመለስ ሆነ፡፡
ኦሮሞዎች ማካሆሬ በተባለችዉ ንግስት አማካኝነት አካባቢዉን ሲወሩ ከፋዎች ከጎጀብ ማዶ ሸሹ፡፡ከኦሮሞ ወደ ደቡብ ምዕራብ መስፋፈት የጀመረዉ በ18ኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን ሲሆን የከፋዉ ንጉስ አስተዳደር ግን ከመካከለኛዉ እስከ 19ኛዉ ክፍለ ዘመን በአከባቢዉ የግቤ እናሪያን ጠቅልሎ ገናና እና ጠንካራ መንግሥታዊ መዋቅር ይዞ የዘለቀ ነዉ፡፡ የአሁኑ ጂማ እና እናሪያ ሕዝቦች በከፋ ንጉስ በሆቲ ሄሮች የአገዛዝ ዘመን በአስተዳደሩ ሥር ነበሩ፡፡በወለጋ አንፍሎ፣ሻካ ፣በደቡብ ምዕራብ አትዮጵያ ሽናሻ፣ ቤንሻንጉል ጉምዝ በዐማራ እና በኦሮሞ ክልሎች የሚገኙ የከፋ ወይም ጎንጋ ህዝብ አካል ናቸዉ፡፡
ከ1790 እስከ1821 ዓ.ም ከፋ በደጋዉ አካባቢ ከነበሩት መንግስታት ሁሉ የላቀ ኃይል ነበረዉ በመሆኑም አርባ ነገሥታት እና ባላባቶች ለከፋ ንጉስ አስተዳደር ግብር ይከፍሉ ነበር፡፡
( በአቶ በቀለ ወልደማርያም የከፋ ህዝቦች አጭርታሪክ ገጽ95)
ኦሮሞዎች በሱማሌ እና በባንቱ ጎሳዎች ተከታታይ ግፊት ወደ መደወላቡ ፈልሰዉ መኖር ከጀመሩ ጀምሮ በሰላም ኢኮኖሚያቸዉ ዳብሮ በአስተማማኝ ለመኖር ገዳ የተባለ ተቋም መሰረቱ፡፡ አባዱላ የተባለዉ የጦር አዝማች የገደ ሥርዓት አካል የሆነዉ ወላቡ እያሉ ሱማሌዎችን ማጥቃት በጀመሩበት ጊዜ የተፈጠረ መዋቅር ነዉ፡፡ይልማ ዴሬሴ1999ዓ.ም፣325 ገዳ ቁጥር እየጨመሩ ለመሄድ ኦሮሞ በተከታታይ ዘመቻ ሰፋፊ እና ለም መሬቶችን መያዝ እና ጠላትንም እየማረኩ በነሱ ሥር ማዋል እዲቻል ወታደራዊ ተቋም /ድርጅት/ ነዉ እየአንዳንዱ የጋላ ወንድ ልጅ በየ8 ዓመቱ ዕድሜ በአምስት እርከኖች ይደራጃል፡፡
እነሱም
1 ከ8 እስከ 16 ዓመት ዐድሜ የሚደራጅበት ደባሌ ይባላል፡፡
2 ከ17 እስከ 24 ዓመታ ዕድሜ የሚደራጅበት ፎሌ ይባላል፡፡
3 ከ25 እስከ 32 እድሜ የሚደራጅበት ቆንዳላ ይባላል፡፡
4 ከ33 እስከ40 ዓመት ዕድሜ የሚደራጅበት ዶሬ ይባላል፡፡
5 ከ41እስከ 48 ዓመት ዕድሜ የሚደራጅበት ሉባ ይባላል፡፡
ከስራ ክፍፍል አንጻር ገዳ ማህበረሰብ የመምራት ሀላፊነት ሲረከብ በሚከተሉት ስሞች ይጠራል፡፡ምችሌ የነበረዉ መጠሪያ ኪሎሌ ይባላል፡፡
ሙደነ ይባል የነበረዉ ሙሉዓታ ይባላል፡፡ሮቤል ይባል የነበረዉ መጠሪያ ቢፎሉ ይባላል፡፡ ሜልቦ የነበረዉ መጠሪያ ዱሉ ይባላል፡፡ቢርመጂ ይባል የነበረዉ መጠሪያ ሆረቲ ይባላል፡፡ የስልጣን እርክክቡ ሥነ ሥርዓት ቡታ ይባላል፡፡ዕድሜዉ ከ40 ዓመት በላይ የሆነዉ ቡድን ምችሌ ይባላል፡፡
አራቱ የጋላ ነገዶች በአንድ ጊዜ አይወሩም ይህም የጦረነቱ ስልት ነዉ፡፡ በወረራ መሪዉ የከረዮ ነገድ ነዉ፡ ፡ሦስቱ ነገዶች ቱሉማ፣ ሜጫእና ወሎ ከመዳወላቡ እና ከአዳነቤ አልተንቀሳቀሱም፡፡
ከ1524 እስከ 1544ዓ.ም ጋሎች የአደረጉት ወረራ መስፋፋት የተፈጸመዉ በከረዮ ነገድ አባላት ነዉ፡፡የከረዮ ነገድ አባላት ባሌን፣ ሀረርጌን፣ወረዉ በያዙበት ወቅት የሜጫ፣ቱሉማ እና ወሎ ነገድ አባላት ለወረራ በሚያደርጉት ስምሪት እዱ ከሌላዉ እዳይጋጭ የሦስቱ ነገድ ሉባዎች ጉባኤ ተቀምጠዉ መዉረር የአለባቸዉን አካባቢ በዕጣ ለዩ እና በዕጣዉ መሰረት ከአዋሽ ወንዝ በስተስሜን የሚገኘዉ አገር ለቱሉማ ነገድ ከአዋሽ ወንዝ በስተምዕራብ እና በስተደቡብ የአለዉ አገር ለሜጫ ነገድ ደረሰ አካባቢዉ ዳሞት እናሪያ፣ቢዛሚን የዛረዉ ኢሊባቡር፣ወለጋ እና ከፋ የሚባሉት ናቸዉ፡፡
ዳሞት የሚባለዉ በዐባይ እና በአዋሽ ወንዝ መካከል የሚገኘዉ ሰፊ የኢትዮጵያን አካል የሚሸፍን ነዉ፡፡ ቢዛምን ዛሬ ወለጋ የሚባለዉ ሲሆን በዳሞት እና በቢዛምን ነዋሪ የነበሩት ህዝቦች ጋፋት እና ዲና የሚባሉ የእናሪያ ነገድ ይኖሩበት የነበረ፡፡ከአዋሽ በስተምስራቅ የአለዉ አገር ለወሎ ነገድ ደረሰዉ፡፡ይህ ዛሬ ወሎ ተብሎ የሚጠራዉ በጊዜዉ አንጎት፣ ላኮ መልዛ ፣አማራ ሳይንት ወዘተ ይባሉ የነበሩትን አካባቢዎች ያጠቃልል ነበር፡፡
የሜጫ ነገድ ወረራከ1304 እስከ 1334 ዓ.ም በአምደ ጽዮን ጊዜ ነበር ለወረራ እናሪያ ዉስጥ በጌዶ አና በቢሎ መካከል የምትገኘዉን ጡጤ ብስል ምትባል ጉብታ ለሰፈራ መረጡ፡፡በዚህ ወረራ የእናሪያ ነገዶች ተሸነፉ ሞቱ ወደ እነሱ ተለወጡ ወደጎጃም ተሰደዉ ዳሞት ኖሩ፡፡
ይልማ ዴሬሴ1999 ሜጫዎች ከጡጤብስል ከጊቤ እናሪያ እስከ ትልቁ ጊቤ ወንዝ ጡጤ ገንበል ድረስ ሰፍረዉ ሌላዉን ፈጅተዉ ለአምስት ተዉልድ ያህል ከቆዩ በኋላ ሰላም ሲያገኙ ቁጥራቸዉ ሲጨምር አካባቢዉን ወሮ ለመያዝ እራሳቸዉን በንኡሳን ጎሳዎች በመከፋፈል ይዞታቸዉን ለማስፋፋት ወስነዉ ተነሱ፡፡
ከጡጤ ብስል በስተስሜን እስከ ግንደ በረት የአለዉን አካባቢ የጤሊያና የሊቨን ጎሳዎች እንዲይዙ፡፡ከጊቤ እስከ ቱሉዋላል አለዉን አካባቢ የሊቃ ጎሳ እንዲይዝ፡፡ የሁሌ እና የጂማ ጎሳዎች በህብረት ከጡጤ ወደ ደቡብ ተጉዘዉ የአለዉን አገር እንዲይዙ፡፡ እነዚህ ጎሳዎች ዲማን፣ ጎማን፣ ሊሙን፣ እናሪያን እና ጉማ የተባሉትን አምስቱ የጊቤን መንግሥታት መሰረቱ፡፡አካባቢዉን ወለጋ አሉት፡፡የሁሌ ጎሳ ከባሮ ወንዝ እስከ ዴዴሳ የአሉን የአንፊሎ ሞቲዎች ግዛት የነበረዉን ወሮ ያዘ ፡፡ከሞት የተረፉት አባይን ተሸግረዉ ወደ ዳሞት እና ወንበራ ተሰደዉ ሰፈሩ አንፊሎ የሚባሉትን ነዋሪዎች ወረዉ ጨፍጭፈዉ ቀሪዎቹን በሜዲቻ/ሞጋሳ/ ማንነታቸዉን አሰቀየሯቸዉ ኦሮሞ ሆኑ ፡፡እነዚህን ገባር የሚል ስም ሰጧቸዉ፡፡ይልማ ዴሬሴ 1999 2ኛ እትም በሰዮ እና በቄለም መካከል ወለል ብለዉ የሰየሙት ተራራ እንደ ወለቡ ሁኖ ስለአገኙት ዋና ከተማቸዉ ጡጤአቸዉን በማድረግ የቡታ በአላቸዉን ማክበሪያ እና የአምላክ ስፍራ አደረጉት፡፡ቀጥሎም በዴዴሳ እና በጊቤ ወንዝ በስተምዕራብ የአለዉን እናሪያን/ኢሊባቡርን/ በቁጥጥር ሥር አደረጓት ሰዎችን /እናሪያዎችን ሚዴቻ እያሰሩ ገባር የሚል ስም ሰጧቸዉ፡፡ ማንነታቸዉንም አጥፍተዉ አሮሞ አደረጓቸዉ፡፡
የወሎ ነገድ የወረራ ዘመቻ በ1554 ዓ.ም የወሎ ነገድ ቡታ አድርገዉ ሉባዎች የሥልጣን እርክክብ በማድረግ ለረጂሙ የስሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ ወረራ ተዘጋጀ ለወረራዉ ተመርቁ ሃላፊነቱን የወሰደዉ
ሀንፋፉ/ዲሉ/ ይህን አባ ባህሪይ ሀርሙፋ ይሉታል የሰየሙትም ገዳን ነዉ፡፡ይህ ገዳ ወሎ ብሎ የሰየመዉ ጥንተ አነጎት፣ላኮመልዛ፣አማራሳይንት በመባል የሚታወቀዉን ወሮ ለመያዝ በአደረገዉ የወረራ ጉዞ ኮቲሲኖ ከምትባል ቦታ ሲደርስ ገወርጊስ ሀይሌ በመባል የሚታወቀዉ ጦርነት ገጥሞ በግራኝ ተዳክሞ ስለነበር ተሸነፈ፡፡የወሎ ጋላ/ኦሮሞ/ ወደስሜን ተጉዞ በአንጎት አዉራጃ ደጋ ላይ ሰፈረ፡፡ በ1554 ዓ.ም ከ አንጎት በስተደቡብ ያለዉ ወሮ በመያዝ ስሙን በዋና ጎሳቸዉ መጠሪያ ወሎ ብለዉ ሰየሙት /ቀየሩት/ ወረራዉን በማስፋፋት የጁን እራያን፣ጋንዝን እና ሳይንትን ወሮ ያዘ ፡፡ወሮባቦ፣ወሮሂሉ ወሮሂመኑ፣ቃሎ ወዘተ የመሳሰሉትን ቦታዎች ስማቸዉን ለዉጦ በነገዳቸዉ መሪ ስም ጠሯቸዉ፡፡ የኦሮሞ ባላባት ሴት ወይዘሮዎች ለጤና ተብሎ ቅንድቡ የገጠመ ወንድልጅ ተፈልጎ በልጁ ደም ይታጠቡ ነበር፡፡በዚህ ምክንያት ልጆች ይጠፉ ነበር ልጅ የጠፋባት እናት እንዲህ ብላ አለቀሰች፡፡
ባልሽ መሀመድ አሊ አንች ማንአለብሽ፣
በየትኛዉ ዳኛ አቤት ልበልብሽ፡፡
ብላ አንዳለቀሰች ታሪክ ይነግረናል፡፡ ማን አለብሽ የተባለችዉ የኦሮሞ ሴት የአማረን ልጅ ለጤናዋ ብላ ታርድ ነበር፡፡ይህ ብቻም አልነበረም የኦሮሞ ወይዘሮወች ሲሞቱ የሴት አገልጋይወች ከነነፍሳቸዉ አብረዉ ይቀበሩ ነበር፡፡
የቱሉማ ነገድ የወረራ ዘመቻ የከረዮ ነገድ ከወለቡ ወደምስራቅ፣ የሜጫ ነገድ ወደ ምእራብ፣ የወሎ ነገድ ወደስሜን ምስራቅ፣ ወረራቸዉን እንዲያሰፉ ሲደረግ፤ የቱሉማ ነገድ አዳነቤን አለቀቀም ነበር፡፡ የቱሉማ ነገድ በ1562 ዓ.ም የዛሬዉን ሽዋን አጠቃለዉ ለመዉረር በአደረጉት ዘመቻ ዘረ ዮሀንስ የተባለዉ ንጉስ ለመግታት ሞክሮ ተሸነፈ፡፡የቱሉማ ነገድ በመገስገስ ሽዋን ይዞ ጎጃም ድረስ ተስፋፋ የዘመኑ መሪ አጼ ሚናስ መግታት አልቻለም፡፡ የሚናስ ልጅ ሰርፀ ድንግል በ1567 ዓ.ም የቱሉማን ወረራ ድል አድርጎ መለሰ፡፡ በዚህ ጦርነት ምንም ሳይተርፍ ጋሎች አለቁ፡፡ ከ10 የማይበልጡ ተርፈዋል የሚሉ አሉ፡፡ አጼ ሰርፀ ድንግል እና ተከታይዎቹ ነገሥታት ጋሎች በአሉበት ሁነዉ ለማዕከላዊ መንግሥት እንዲገብሩ እራሳቸዉም ማዕከላዊ ምግሥት አባል ሁነዉ የአገሪቱን አንድነት እና የግዛት ክልል ከወራሪ እንዲጠብቁ አደረጉ፡፡ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ሃይሌ 1997፣85
የቱሉማ ዘመቻ ከባሌ እስከ ሽዋ እና ጎጃም በአደረገዉ ወረራ ጥንት ነዋሪ ነገዶችን አጥፍቶ እና ማንነታቸዉን አሰለዉጦ መራቤቴ፣መንዝ፣ይፋት እና ጥሙጋ ወዘተ ነዋሪን ከሰፊዉ እና ለም ቦታ አባሮ ይኸዉና ዛሬ እንደ ዝንጀሮ ዳገት ሲቧጥጥ የሚታየዉ በቱሉማ ነገድ ወረራ ሸሽቶ የሄደ ለመሆኑ ማሳያ ነዉ፡፡ጋሎች መቶ አመት ባልሞላ ጊዜ ዉስጥ ዛሬ ሀረርጌ፣አሩሲ፣ባሌ፣ሲዳሞ ፣ከፋ፣ኢሊባቡር፣ወለጋ ፣፣ ሽዋ፣ወሎ እና ጋሙጎፋን በሙሉ ወረዉ ትግራይ እና ጎጃም ድንበር ድረስ ተጉዘዉ ተጽእኖአቸዉን ለማሳረፍ ያስቻላቸዉ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸዉ፡፡
1 በግራኝወረራ ህዝቡን ማሰባሰብ ማደራጀተ መምራት የሚችሉ የነገዱ ጀግኖች መሪዎች ሽንብራ ኮሬ ላይእና በ15 ዓመት ጦርኘቶች ማለቃቸዉ እና ተተኪ ለመፍራት ጊዜ አለማግኘታቸዉ ፡፡
2 ንጉሶች ሲሞቱ ወይም ከሀላፊነት ሲወገዱ ይተኩ የነበሩት ለዑላን እና መሳፍንቶች ግራኝ ግሼ አምባን በወረረ ጊዜ ሁሉንም አርዶ ስለጨረሳቸዉ፡፡
3 ኦሮሞዎች( ጋሎች)የገዳ ሥርዓታቸዉን አጎልብተዉ ለዓመታት ወጣቱን በወታደራዊ እዝ ቁጥጥር ሥር አዉለዉ ወረራን ብቸኛ የግዛት ማስፋፊያ አድርገዉ መያዛቸዉ እና ወንድ የሆነዉን የነገዱን አባል በሙሉ ተዋጊ ማድረጋቸዉ፤
4 ኦሮሞዎች ለወረራ የተመቻቸዉ ገራኝ አህመድ በጅሀድ ጦርነት ዐማሮችን እና ክርስቲያኑን ሕዝብ ስለአዳከማቸዉ እንደሆነ ዶናልድ ሊቨን አባ ባህሪይ የጋላ ታሪክ ሲሉ በጻፉት መጽሀፍ የአቀረቡትን ይስማማበታል፡፡ጋሎች ለጦርነት የሚገፋፋቸዉ ይህን እንዲያደርጉ የሚያደርጋቸዉ የጠነከረ ባህል ስለአላቸዉ ነዉ፡፡ኦሮሞዎች (ጋሎች) ሰዉ ወይም ትልቅ አዉሬ የገደሉ እንደሆነ ከአናታቸዉ ጥቂት ጋሜ አስቀርተዉ ፀጉራቸዉን ይላጫሉ፡፡ሰዉ ወይም ትልቅ አዉሬ ያልገደለ ስለማይላጭ ቅማል ያሰቃየዋል፡፡ ሊፈጁን የሚሻሙትም በዚህ ምክንያት ነዉ፡፡(ሚሊዮን ነቅንቅ ትርጉም1993፣80)
በሌላ በኩል ወረራዉ የሚፈጸምባቸዉ ነገዶች በተለይም ዐማራዉ በአስር መደቦች የተከፋፈለ ነበር፡፡ ከአስሩ ዉስጥ ዘጠኙ ጦርነት የማይሄዱ ሲሆን ተዋጊዉ አስረኛዉ መደብ ብቻ ነበር፡፡ 1 መነኩሴ 2 ደብተራ 3 ዳኞች 4 የመኳንንት ሚስቶች፣ወይዛዝርቶች እና ደጋፊዎች 5 ሽማግሌዎች 6 ገበሬዎች 7 ነጋዴዎች 8 አንጥረኞች እና ጸሀፊዎች 9 አዝማሪዎች እናላሊበላዎች 10 ጋሻ የሚይዙ፣ዉጊያ የሚችሉ፣ ወታደሮች ፕሮፌሰር ጌታቸዉ ሃይሌ 1997፣90
በኦሮሞ በገዳ ሥርዓት ወንድ ልጅ ተደራጅቶ ዋና ሥራዉ ጦርነት ማህበረሰቡን በዉትድርና ማገልገል ነዉ፡፡ ይህም ባህል ሆኖ በመዝለቁ ሁሉም ወንድልጅ ለዉጊያ መሰለፍ ፣ለጦርነት መዘጋጀት የዉዴታ ግዴታዉ ነዉ፡፡ ከሁሉም በላይ ይህ የዉዴታ ግዴታ ሚስት ለማግባት ከአለዉ ፍላጎት ጋር ሲቀናጅ ዉጤቱ ጋላ ያልሆነዉን ሁሉ ለመግደል የሚፈጥረዉን መነሳሳት መገመት ይቻላል፡፡ በዚህ ምክንያት ሁሉም የጋላ ጎረምሳ የሚከተሉት ጥረት ነዉ፡፡ሚስት ለማግባት ከአለዉ ፍልጎትጋር ሲደመር 1 የመስፋፋት ዓላማ በሃይል እና በጦርነት በማካሄድ ወረራ የተካሄደባቸዉን አካባቢዎች ነገዶችን መግደል 2 እየአንዳንዱ የገዳ አባል ጀግና የሚባለዉ ፀጉሩን ተላጭቶ ከቅማል በመዳን የፈለጋትን ሴት ማግባት ሲችል ነዉ፡፡ይህ ሊሆን የሚችለዉ ደግሞ ትልልቅ አዉሬዎችን ሲገድል እና ከጎሳዉ ዉጭ የሆነ ሰዉ ገድሎ፣ ሰልቦ ሲያቀርብ ነዉ፡፡
አባቶቻቸዉን የገደሉባቸዉን ልጆች ለነሱ ከብት ጠባቂ እና አገልጋይ ለማድረግ በጉዲፈቻ አሳድገዉ ማንነታቸዉን በማስለወጥ ኦሮሞ ማድረግ፤
ወረዉ የያዙትን አካባቢ የጥንት ነዋሪ ነገዶችን ሞጋሳ በሚሉት የማንነት ማጥፊያ ባህላቸዉ በማጥፋት የኦሮሞን ባህል እና ቋንቋ አሰገድደዉ እንዲቀበሉ በማድረግ ፤
በዚህ ሂደት በኦሮሞ ወረራ የተፈጁትን፣የተቀላቀሉትን፣ተገደዉ የተባረሩትን ህዝቦች ማን ማን እነደሆኑ ብዛታቸዉን እና ማንነታቸዉን በአሀዝ ለይተን ባናዉቅም፡፡በደቡብ ኢትዮጵያ ሴማዊ ቋንቋ የሚናገሩትን አርጎባዎች፣ስልጢ፣ጉራጌዎች፣ጋፋት እና ዐማሮች ከመጠን በላይ የአለቁ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል፡፡
ከ1605 እስከ1617ዓ.ም የጋሎች ወረራ ወደስሜን መዕራብ ቀጥሎ የቦረና ኦሮሞዎች በጌምድርን እናጎጃምን ወረዋል፡፡ ከ1620 እስከ 1658/20፣27፣36፣39፣43፣49፣52፣58ዓ.ም/ እና በተከታታይ ኦሮሞዎች ለመዉረር የአደረጉትን ዘመቻ የክሪስቲያን መንግሥት ለመመከት አልቻለም፡፡በ1684/85/ዓ.ም እኤአ ቀዳማዊ እያሱ ከወሎ እና ከጎጃም የኦሮሞ ወራሪዎች ጋር ጦርነት ገጥመዋል፡፡በ1693/4/ዓ.ም የጉዱሩ አሮሞ ጎጃምን እና በጌምደርን ወረዋል፡፡ (አለማሁአበበ ትርጉም 2003፣193)
በ16ኛዉ ክፍለ ዘመን አሮሞዎች ከደቡብ ኢትዮጵያ ወደ ስሜን እና ምስራቅ ጎርፈዉ ብዙዉን ደጋ አገር ይዘዉ ሰፍረዋል፡፡(ይልማ ዴሬሴ በገጽ12) በግራኝ ወረራ የተዳከመዉ የሀበሻ መንግሥት ሳያገግም የኦሮሞ መስፋፋት ብለዉ የሚጠሩት ዛሬ ኢትዮጵያ ብለን በምንጠራዉ መንግሥታዊ ግዛት ዉስጥ በሁሉም አቅጣጫ ተካሂዶ የዚህ የኦሮሞ ግንድ እስከ ወሎእና ጎንደር ደርሶ እኤአ ከ1769 እሰከ 1855ዓ.ም ዓ.ም
ከየጁ ኦሮሞ የተወለደ መሳፍንት የየጁን ሥርዎ መንግሥት ጎንደር ላይ መሰርቶ ከ80 ዓመት በላይ ቆየ ሲል የኦሮሞን የወራሪነት ታሪክ በመጽሀፉ አስፍሯል፡፡
በ1855 ዓ.ም ቴዎደሮስ ነገሠ፡፡ የአካባቢ መሳፍንቶችን እናየጦር አበጋዞችን ከአስገበረ በኋላ፤የኢትዮጵያን አንድነት መልሶ ለመገንባት የጎንደርን ፣የጎጃምን፣የትግራይን፣የወለጋን እና የሽዋን መሳፍንት ለማሰገበር ተነቀሳቀሰ፡፡ ቴወድሮስ ይህን ኢትዮጵያን አንድ ለማድረግ ዘመቻ በጀመረበት ወቅት በእንግሊዝ ግዛት ፀሀይ አትጠልቅም የሚባልበት ዘመን ስለነበር፤ ትወድሮስ ከአንግሊዝ መነግሥት ጋር በገቡት ጠብ ከህንድ በተንቀሳቀሰዉ እና በናፒየር በተመራዉ ጦር መቅደላ ላይ ድል ሆኑ፡፡ ለናፒየር ድል ማድረግ እና ለቴዎድሮስ ድል መሆን ወሳኙን ሚና የተጫወተዉ የዚያን ጊዜዉ የደጃዝማች ካሳ ምርጫ የኋላዉ አጼ ዮሀንስ 4ኛዉ ለስልጣን ሲል ቴወድሮስን ሊወጋ የመጣዉን የእንግሊዝ ጦር መንገድ መሪ፣ሥንቅ አቀባይ እና መረጃ ሰጭ ሆኖ በመሰለፉ ነዉ፡፡
ከቴወድሮስ ኅልፈት በኋላ ወደ ሥልጣን የወጡት ገበዜ ገብረ-መደኅን(ዳግማዊ አጼተክለ ጊዮርጊስ) ናቸዉ፡፡ተክለ ጊዮርጊስ ከ1860 አስከ1863 ዓ.ም የቴወድሮስን ዓላማ በመያዝ ኢትዮጵያን አንድ የማድረጉን ዓላማ ገፉበት፡፡ ሆኖም በ1863 ዓ.ም የናፒየር ተባባሪ ሁኖ ለቴወድሮስ ኅልፈት ወሳኙን ሚና የተጫወተዉ ካሳ ምርጫ ከናፒየር በተሰጠዉ የጦር መሳሪያን ወታደራዊ አስተማሪ ኃይሉን አደራጅቶ በእህቱ ባለቤት በዳግማዊ አጼተክለ ጊዮርጊስ ላይ ዐመጸ ፡፡ በዐመጹ ገፈቶበት በ1863 ዓ.ም ዐደዋ ዉስጥ አሰም ወንዝ ዳርቻ ሁለቱ የስልጣን ባላንጣዎች ጦርነት ገጥመዉ ድል የካሳ ምርጫዉ ሆነ፡፡
ካሳ ምርጫዉ ተክለጊዮርጊስን ድል አድርገዉ እስረኛቸዉ ከአደረጉ በኋላ፣ዘዉድ ጭነዉ አጼዮሀንስ 4ኛዉ በመባል ነገሡ፡፡ ዮሀንስ ከ1863 እስከ 1881 ዓ.ም በአሉት ዓመታት ኢትዮጵያን አንድ በማድረግ የቴወድሮስን ዓላማ ገፍተዉበታል፡፡ በተለይም በዚህ ዘመን በቱርክ እየተረዱ ግብፆች የአደረጉትን ተከታታይ ወረራዎችን በመመከት የኢትዮጵያን አንድነት እና ለዓላዊነት አስከብረዋል፡፡ ያምሁኖ ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛት ለመያዝ የአሰፈሰፈችዉን ጣሊያንን ከምጽዋ እና ከአሰብ ገፍትረዉ ያላስወጡ በመሆናቸዉ፤ ለእርሳቸዉ ኅልፈት ምክንያት ወደሆነዉ የድርቡሽ ወረራ ፊታቸዉን ወደ መተማ በአዞሩበት ወቅት፤ ጣሊያን አስመራን በመቆጣጠር ባህረ ነጋሽ ይባል የነበረዉን ግዛት ኤርትራ የሚል ስም ሰጥታ የቅኝግዛቷ አካል አደረገች፡፡ ዮሀንስም ከድርቡሾች ጋር በአደረጉት ጦርነት ኅይወታቸዉ አለፈ፡፡ ይህም በአገሪቱ እምብርት ላይ ሁነዉ ለሥልጣን ሲያደቡ ለነበሩት ንጉሥ ምኒልክ ወደ ሥልጣን እንዲመጡ ምቹ ሁኔታን ፈጠረላቸዉ፡፡
ምኒልክ ከ1881 አስከ 1913ዓ.ም እኤአ በቆየዉ ሥልጣናቸዉ በቴወድሮስ ዓላማ በመግፋት በአጼ አምደጽዮን ዘመን የነበረችዉን የኢትዮጵያ ግዛትመልሰዉ የአዋቀሩ ንጉሠ ነገሥት ናቸዉ፡፡ምኒልክ የኢትዮጵያን አንድነት ከማሰከበር ጎን፤በ1888 ዓ.ምአድዋ ላይ ከጣሊያን ቅኝ ገዥ ኃይል ጋር ገጥመዉ ድል በመንሳት ኢትዮጵያ የጥቁሩ ዓለም ሕዝብ የነፃነት ቀንዲል ሁና እንድታበራ ከማድረጋቸዉ በአሻገር፤ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ከቅኝ ገዥ ኃይሎችጋር ተደራድረዉ የተከላከሉ ብልሕ ንጉሥ ለመሆናቸዉ ዓለም የመሰከረላቸዉ ናቸዉ፡፡
ምኒልክ የግራኝን ወረራ ተከትሎ የመጣዉን የጋላ(ኦሮሞ)ወረራ፤ሁሉንም ተቆጣጥሮ ለከብቶች እረቢ የሚሆን ሰፊ መሬት መያዝ፣ ጠላቴ ነዉ በሚለዉ ነገድ ላይ ዘምቶ በኃይል በሞጋሳ እና በጉዲፈቻ ኦሮሞ ማድረግ እንጂ፤መንግሥት መመስረት ፍላጎትም ሆነ ዓላማ ያልነበራቸዉ ጋሎች በቀላሉ የግዛታቸዉ አካል ለማድረግ ጊዜ አልወሰደባቸዉም፡፡ በመሆኑም መላዉ አገሪቱን በአራት ነገዶች ተከፋፍለዉ ወረዉ የነበሩትን የከረዮ፣የመየጫ፣ የወሎ እና የቱሉማ ጎሳዎች ወረዉ የያዙትን አካባቢ አንድ ወጥ ማዕከላዊ መንግሥት ለመመሥረት አልሞከሩም፡፡ለመስፋፋት መሳሪያ የሆናቸዉን ገዳን ከማዳበር ተቆጥበዉ
በደረሱበት ማኅበረሰብ ባህል ተዋጡ፡፡የገዳን ሥርዓት ለወታደራዊ ወረራ እንጂ፣ለመንግሥት አመራር በሚያስችል መልኩ ማደራጀት አልሞከሩም፡፡
የከረዮ ነገድ ሐረርጌን፣ባሌን እና አርሲን ከተቆጣጠረ በኋላ፣አካባቢዉን በአንድ ማዕከላዊ አሰራር ለማደራጀት አልሞከሩም፡፡ ከሁሉም በላይ ሐረር ግንብ ዉስጥ የመሸገዉን ኢሚር ከምሽጉ አስወጥቶ ከተማዉን ለመቆጣጠር ባለመሞከሩ፣በሐረር ከተማ የኢሚር የበላይነት እስከ ምኒልክ የጨለንቆ ዘመቻ ድረስ እንዲቀጥል ዕድል የሰጠ ነበር፡፡ በደቡብ የጋሎች ወረራ፣ወላይታዎችን፣ ሐዲያዎችን፣ከምባታዎችን፣ ጉራጌዎችን፣ሲዳሞዎችን ወዘተ ይዞታቸዉን በማጥበብ የነገዶችን ማንነት በመለወጥ፣ የጋላን ማንነት እንዲይዙ አድርጓል፡፡ ይኸም ሆኖ፣በደቡብ የነበሩት ልዩልዩ ነገዶች የየራሳቸዉን ማንነት ለማስጠበቅ የአካባቢ ማዕከላዊ መንግሥት ከመመስረት አላገዳቸዉም፡፡ ከነዚህም ጎልቶ የሚታወቀዉ የወላይታዉ ካዎ የሚባለዉ ንጉሥ አንዱ ነበር፡፡
በደቡብምዕራብ የዘመተዉ የሜጫ ነገድ፤የዛሬዉን ወለጋ(ቢዘምን) እናዳሞት እንደገባ እራሱን በንዑስ ነገዶች አደራጅቶ ሊቃ ቄለም፣ሊቃ ለቀምት እና ጂማ በሚባሉ ማዕከሎች እራሳቸዉን የሚያስተዳድሩ አካላትን ፈጠረ፡፡ የጊቤ መንግሥታት በመባል የሚታወቁት ለሙ፣እናሪያ፣ ጉማ ፣ጂማ፣ጎማ እና ጌራ የተሰኙ ትናንሽ የአካባቢ መንግሥታት መስርተዉ ይተዳደሩ ነበር፡፡ ዋናዉ የኢኮኖሚ ምንጫቸዉ የባሪያ ንግድ ስለነበር፤ የሜጫ ነገድ አባላት እንደ ጃንጃሮ፣አንፍሎ፣ዐማራ፣ሜያ፣ከፍቹ፣ቱርማ ወዘተ የመሳሰሉት ነባር ማኅበረሰቦች ባሪያ በማድረግ ወደ ዛንዚባር አሻግረዉ በመሸጥ ኢኮኖሚያቸዉን ያዳብሩ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ የደቡብ ምዕራብ እና የደቡብ ምስራቅ አካባቢ ልክ እንደ ሽዋ እና እንደስሜኑ በመካከሉ ሰላም አልነበረም፡፡ለግጦሽመሬት ፍለጋ እና ሰፊ የባሪያ ገበያ ለማግኘት አንዱ ከሌላዉ ጋር ሲዋጋ ኖሯል(ዶ/ርላጲሶ ጌ ዴሊቦ ገጽ 329—339
ይህን የዶ/.ር ላጲሶ ጌ ዴሌቦን ሀሳብ በማጠናከር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ጋሎች በወረራ የያዙትን አካባቢ ማኅበረሰብ ለቱርክ በባሪያነት በገፍ መሸጣቸዉን ከማረጋገጣቸዉ ጎን በሞጋሳ እና በጉዲፈቻ ማንነታቸዉን ያጡ ነገዶች ቁጥር 28 መሆናቸዉን አረጋግጠዋል፡፡በማያያዝም በምዕራብ ወለጋ በስዩ አካባቢ ብቻ በግዳጅ በሞጋሳ ማንነታቸዉን የአጡ ነገዶች 13 እንደሆኑ በ1984 ዓ.ም ለዶክትሬት ድግሪ መመረቂያ በአዘጋጁት ጥናታዊ ጽሁፍ የጠፉትን ነገዶች ስም በመዘርዘር አረጋግጠዋል፡፡
አደዋ ላይ የላቀ ሚና ከተጫወቱት የጦር መሪዎች እቴጌ ጣይቱ እና ወንድማቸዉ ወሌ ብጡል፣እራስ ሚካኤል /መሀመድ አሊ/ የእያሱ አባት የአምባልጌዉን የጣሊያን ምሽግ የደመሰሱት የጦር ሚኒስቴሩ ፍታዉራሪ ገበየሁ ተክሌ፣ ለዑል እራስ መኮነን ወልደሚካኤል፣ የጎጃሙ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት፣ደጃዝማች ባልቻ እና ፍታዉራሪ ሀብተገዎርጊስ ዲነግዲ የኦሮሞ ዝርያ የአላቸዉ እንደሆኑ(ደ/ር መራራ ጉዲና ምስክርነታቸዉን) ሰጥተዋል፡፡
በዚህ የተቆላለፈ እና የተጠላለፈ ሂደት ያለፈዉን እና ያለዉን ሕዝብ ለመነጣጠል የዛሬዎቹ የኦሮሞ ፖለቲከኞች በአለፉት አራት መቶ ዓመታት ከሀረርጌ አስከ ጎንደር፤ከቦረና እስከ ትጋራይ የአለዉን ማህበረሰብ ወሮ የሚገድለዉን ገድሎ፤ የሚሰደደዉን አሰድዶ፤ ቀሪዉን በጉዲፈቻ እና በሞጋሳ ማንነቱን አስለዉጦ፤ ተጋብቶ እና ተዋልዶ የአለዉን ሕዝበ ለመነጣተል የሚያደርጉት የጠባብነት ጉዞ ከማስገረም አልፎ የሚያስደንቅ ነዉ፡፡ዛሬ የዓለም ህዝብ በሰከንድ እየተገናኘ አንዱ ነገድ ከሌላዉ ነገድ ዘርእና ቀለም ሳይለየዉ እየተጋባ እየተዋለደ በሚገኝበት ዘመን ፖለቲከኞች ለኦሮሞ ህዝብ ከአንተ በበለጠ ለአንተ እኛ እናዉቅልሀለን በማለት፤ሳይመርጣቸዉ እራሳቸዉን የመረጡ ዶክተር እና ፕሮፌሰር በሚል ማዕረግ የተሸፈኑ ያልተማር መናገር ቀርቶ የማያስበዉን እያሰቡ የኦሮሞ ችግር ከአማራዉ ጋር መጋባቱ ነዉ፡፡ የተጋበህም ተፋታ ወደፊትም ከማንም ጋር የጋብቻ ቅልቅል አንዳታደርግ በተለይ ከአማራጋር እያሉ
የሚቀሰቅሱ እና ትምህርታቸዉን ተቀብለዉ ለሚያስተጋቡ ወጣቶች በሰጡት ትምህርት ፍሬአማነት ተደስተዉ ሲያጨበጭቡ የሚተዩ ሊቀሊቃዉንት መገኘታቸዉ ነዉ፡፡
ዐማራዉ በብቸኝነት ኢትዮጵያን መርቷል ለሚሉ የሀሰት ትርክቶች ማርከሻ ማሳያ፡-
የአማራዉ ገዥ ኢትዮጵያን ፈጥሮ በሱ ሥር ሌሎች ኢትዮጵያዊያንን ጨቁኗል፣በዝብዞአል፣ወዘተ በሚል ኢትዮጵያን ለማጥፋት ሌት ከቀን ለሚባዝኑት የምዕራባዊያን ፀረ ኢትዮጵያ እና ፀረ አማራ የጥፋት መልዕክተኞች እና ደቀመዛሙርቶቻቸዉ የሀሰት ትርክታቸዉን ገላልጦ ማሳያ ማሰረጃ ይሆን ዘንድ የሩቁን ትተን ከንግስት ሳባ ወይም ማክዳ ወይም አዜብ ንግሥና ዘመን ጀምሮ እሰከ ዘመነ ህወሓት (ኢህአዴግ) አገዛዝ የአለዉን መመልከት የትርክቱን ገለባነት ያሳያል፡፡
የኢትዮጵያ ነገሥታት ከንግሥት ማክዳ/ሳባ እስከ ገርሳሞት/ህንደኬ ከ1013—42 ዓ.ም የነገሡ ነገሥታት፡-
ንግስት ሳባ ከ1013 እስከ 982 ዓ›ዓ ቀዳማዊ ምኒልክ ከ982 አስከ 957 ዓ›ዓ
ንድዩን ከ957 አስከ 956 ዓ›ዓ ቀዳማዊ ሲራህ ከ956 አስከ 930ዓ›ዓ
አሜንሆቴፕ ከ930አስከ 889ዓ›ዓ አክሱማይራሚሱ ከ889አስከ869 ዓ›ዓ
ሲራህ ዳግማዊ ከ869 አስከ 831ዓ›ዓ ተዋሲያ ዳግዊ ከ831አስከ810ዓ›ዓ
አብራሊልዮስ ዳግማዊ ከ810 አስከ778 ዓ›ዓ አክሱማይ ወረደ ጸሀይ ከ778 አስከ 755 ዓ›ዓ
ካስህታ አንድዮን ከ755 አስከ742 ዓ›ዓ ሰባካ ዳግማዊ ከ 742 አስከ 730 ዓ›ዓ
ኒካንታ ቅንዳኬ ዳግማዊ ከ730 አስከ 720 ዓ›ዓ ወረደ ነጋሽ ከ720 አስከ 671 ዓ›ዓ
ኮርድ አሜን ከ671 አስከ 665ዓ›ዓ ገስዮ ከ 665 ዓ›ዓ
ኑአትሚአሙንከ665 አስከ661 ዓ›ዓ ቶማድዮን ሳልሳዊ ከ661 አስከ 649 ዓ.ዓ
አሚነአስሮ ዳግማዊ ከ649 አስከ 633 ዓ›ዓ ፒያንኪያ 4ኛ ከ633 አስከ 599 ዓ›ዓ
ዝዋሬንብረትአሰፑርታ ከ599 አስከ 558 ዓ›ዓ ስይፋይ ሀርሲአተዉ ከ558 አስከ 546 ዓ›ዓ
ረምሀይ ናቶሰናይ ከ546 እስከ 532 ዓ›ዓ ሀንዲዉ አበራ ከ532 አሰከ 521 ዓ.ዓ
ሶፊሊያኒኪቦን ከ521 አስከ490 ዓ›ዓ አግልቡልስዌኮስከ490 አስከ 469
ጵስመረት/ወረደ ነጋሽ/ከ469 አስከ448 አዓ›ዓ አዉሳ ብራኮስ ከ448 አስከ 436 ዓ›ዓ
ቀኒዝጵስሜስ ከ436 አስከ 423 ዓ›ዓ አጵራሶ ከ423 አስከ 413 ዓ.ዓ
ካሽታወልድ እሁሁከ413 አስከ 393 ዓ›ዓ ኤላልዮን ተአንኪከ393 አስከ 383 ዓ.ዓ
አትሲርካሚንሳልሳዊ ከ383 አስከ 373 ዓ›ዓ አትሲርካሚን 4ኛዉከ373 አስከ 363 ዓ›ዓ
ሀዲና ከ363 አስከ 353 ዓ›ዓ አትሲር ከሚን 5ኛዉ ከ353 አስከ 343 ዓ›ዓ
አትሲርካሚን6ኛዉ ከ343 አስከ 333 ዓ›ዓ ኒካዉልቅንዳኬ 3ኛዉ ከ333 አስከ 323
ባሱ ከ323 አስከ 316 ዓ›ዓ ኒካዊላ ቅንዳኬ 4ኛዉ ከ316 አስከ 306 ዓ›ዓ
አዉጥጥ አራዉራ ከ306 አስከ 296 ዓ›ዓ አርካሚን ዳግማዊ ከ296 አስከ 286 ዓ›ዓ
ካላስ ዳግማዊ ከከ286 አስከ276 ዓ.ዓ ዘዋሬ ንብረት ከ276 አስከ260 ዓ›ዓ
ሶትዮ ከ260 እሰከ 246 ዓ›ዓ ሠይፋይ ከ246 አስከ 233 ዓ›ዓ
ኒኮሲስ ቅንዳኬ 5ኛ ከ233 አሰከ 223 ዓ›ዓ ረምሀይአርሚን 4ኛ ከ223 አስከ 213 ዓ›ዓ
ፌልያሁርኔ ከ213 አስከ 198 ዓ›ዓ ሀንዲ አዉኪራራ ከ198 አስከ176 ዓ›ዓ
አግሀቡ ብሴህራን ከ176 አሰወከ 166 ዓዓ ሱላይክዋዉ ሚዉን ከ166 አስከ 146 ዓ.ዓ
መስሊኒ ቁራር ሜር ከ146 እስከ 138 ዓ.ዓ ነግሳይ ብሲኒት ከ138 አስከ128 ዓ.ዓ
ኤትቢኑካዊር ከ128 አስከ 118 ዓ.ዓ ሶፌልያስ አብራሚን ከ118 አስከ 98 ዓ.ዓ
ሶናይከ98 አስከ 88 ዓ.ዓ አወሲና ንግስት ከ88አስከ 77 ዓ.ዓ
ዳዊት ዳግማዊ ከ77አስከ67 ዓ.ዓ አግለ ቡልስ ከ67 አስከ 59 ዓ.ዓ
በዋዉል ከ59 አስከ 49ዓ.ዓ ቢረዋስ ከ49 አስከ 39 ዓ.ዓ
ዳኒዳድ ከ39 አስከ 29 ዓ.ዓ አሞይ መሀሲከ 29 አስከ 24 ዓ.ዓ
ኒኮትሪስ ህንዴኬ6ኛከ 24 አስከ 14 ዓ.ዓ ኖልኪ ከ14 አስከ 12 ዓ.ዓ
ሉዛይ ከ12 አስከ 8 ዓ.ዓ ባዚን ከ8ዓ.ዓ አስከ 8 ዓ›ም ባዚን በነገሰ በ8ኛዉ ዓመቱ ክርስቶስ በቤተልሄም ተወለደ ባዚን ከክርሰቶስልደት በኋላ ዘጠኝ ዓመት ነግሷል ከሳባ አስከ ባዚን በኢትዮጵያ የነገሱ 68 ናቸዉ፡፡
የአኩሱም ሥርዎ መንግስት
አብርሀ ወአጽብሀከ313 አስከ339ዓ›ም አብረሀም ኤዛና ከከ339 አስከ 351 ዓ.ም
አስፍሀ ደልዝ ከ351 አስከ 358 ዓ.ም ሰህለ ከ358 አስከ 372 ዓ›ም አርፍድ /ገ/መስቀል ከ372 አስከ 376ዓ›ም አድህና ንግስት ከ376 አስከ 381 ዓ.ም
ርትዕ ከ381 አስከ 382 ዓ›ም አስፋሀ ዳግማዊ ከ382 አስከ383 ዓ›.ም
አጽብሀ ዳግማዊ ከ383 አስከ 388ዓ›ም አሜዳ ቀዳማዊከ388አስከ 403 ዓ›ም
አብርሀ ደግማዊ 403 አንድ ወር እለ ሳሀል 403 ዓ›ም
እለ ገበዝከ403 አስከ405ዓ›ም ሳህል ከ405 አስከ 409ዓ›ም
አብርሀከ409 አስከ 419 ዓ›ም አድሀና ንግስትከ419 አስከ 425ዓ›ም ዕዮአብከ425 አስከ435 ዓ.ም ጸኀም ዳግማዊ ከ435 አስከ 437ዐ›ም
አሜዳ ዳግማዊ ከ437 አስከ 438 ዓ›ም ሳህል አህዛብ ከ438 አስከ 440 ዓ›ም
ፅባህ/ክርሰቶስ/ ከ440 አስከ443 ዓ›ም ፆሀም ሳልሳዊ ከ443 አስከ445 ዓ›ም
እለገበዝ ዳግማዊከ445 አስከ451 ዓ›ም አጋቤ ከ451 አስከ 452 ዓ›ም
ሌዊ ከ452 አስከ 454 ዓ›ም አሜዳ ሳልሳዊ ከ454 አስከ457
አርማህ ዳዊት ከ457 አስከ 471 ዓ›ም አምሲ ከ471 አስከ 476 ዓ.ም ሶልአደባ ከ476 አስከ 485 ዓ›ም አለሜዳ ከ485 አስከ 493 ዓ.ም
ኤሄና ዳግማዊ ከ493 አስከ 500 ካሌብ ከ500 አስከ530
ዘ እስራኤል 530ዓ.ም ገብሩ 530 ዓ.ም ገብረመስቀል ከ530 አስከ544 ዓ.ም
ቆስጠንጢኖስ ከ544 አስከ 572 ወሰንሰገድ ከ572 አስከ 587 ዓ.ም
ፍሬሰናይ ከ587 አስከ 610 ዓ.ም አድርአዝ ከ610 አስከ 630 ዓ.ም
አካለ ዉድም ከ 630 አስከ638 ግርማ አሰፈር ከ638 አስከ 653
ዝርጋስ ከ653 አስከ 663 ዓ.ም ድግና ሚካኤል ከ663 አስከ 689 ዓ.ም
በህር ኤክላ ከ689 አስከ 708 ዓ.ም ጉም ከ708 አስከ732 ዓ.ም
አሰጉምጉም ከ732 አስከ737 ዓ.ም ለትም ከ737 አስከ 753 ዓ.ም
ትላትም ከ753 አስከ774 ዓ.ም አዳጎሽ ከ774 አስከ787 ዓ.ም
አይዘር 787 ዓ.ም ድድም ከ787 አስከ 792 ዓ.ም ዉድድም ከ792 አስከ 802 ዓ.ም
ዉድማ አስፈሬ ከ802 አስከ 832 ዓ.ም አርማህ ከ832 አስከ 837
ድግናዥን ከ837 አስከ 856 ዓ.ም ግዳዥን ከ 856አስከ 857 ዓ.ም
ጉዲታ ከ857 አስከ 897 ዓ.ም አንበሳ ዉድም 897 አስከ 917 ዓ.ም
ድልነአድ/ማእድይ/ ከ917 አስከ 929 ዓ.ም የማን ወገን እንደሆነች የማትታዎቅ መሪ የሷ ወረራ የአኩሱምን ዉድቀት አስከትሏል፡፡
የዛጉየ ሥርዎ መንግስት
መራ ተክለሀይማኖት ከ927 አስከ 940 ስቡሀይ ድልነአድ 2ኛ ከ940አስከ 950 ዓ.ም
መይራር ከ950 አስከ965 ዓ.ም ሀርበይ ብርሀነመስቀልከ965 አስከ 973 ዓ.ም
መንግሰነ ይባርክ ከ973 አስከ 980 ዓ.ም ይስበክ ዕግዚ ከ980 አስከ 990 ዓ.ም
ዜና ጰየጥሮስ ከ990 አስከ996 ዓ.ም ባህርስፍ ከ996 አስከ 1010 ዓ.ም
ጠጠዉድም ከ1010 አስከ 1020 ዓ.ም አክወቲት ዣን ስዩም ከ1020 አሰከ 1040 ዓ.ም
በእምነት ግርማ ስዩም ከ1040 አስከ 1060 ዓ.ም ይምርሀነ ክርስቶስ ከ1060 አስከ1100 ዓ.ም
ገብረማሪያም ቅዱስ ከ1100 አስከ1140 ዓ.ም ገብረመስቀል/ላሊበላቅዱስ ከ1140 አስከ 1180 ዓ.ም
ነአኩቶለአብ ቅዱስ ከ1180 አስከ1220 ዓ.ም ይትባረክ ከ1220 አስከ1260 ዓ.ም አንዳንዶች የዘጉየ የመጨረሻዉ መሪ ይትባረክ ሳይሆን ነአኩቶለአብ ነዉ ይላሉ፡፡
በሽዋ ሥልጣናዊ ግዛት የማህዙሚ ሥርዎ መንግስት
ባዲት ቢነት ማያ ከ 1063ዓ.ም ሀርቤ ኢርሀርብ አራድ 1108 ዓ.ም
ማልስሜይ ቀዳማዊ 1183 ዓ.ም ሁሰይን ከ1179 አስከ 1180 ዓ.ም
አብደላህ 1193/94/ መሀመድ ኢብን ሁሴይን ከ1235 አስከ 1239 ዓ.ም
ማልዛርህ አብን ከ1239 አስከ1252ዓ.ም ግንባህ ከ 1252 አስከ 1262 ዓ.ም
ጊራም ጋዚ ከ1262 አስከ 1263 ዓ.ም ዲልጋሚስ ከ1263አስከ 1269 ዓ.ም
ዲልማራህ ኢብን ከ1269 አስከ 1278ዓ.ም ዲል ጋሚስ ከ1278 አስከ 1285 ዓ.ም
አብዳላህ ኢብን ከ1279አስከ 1279 ዓም
ከይኩኖ አምላክ ጀምሮ የአሉ የሰለሞናዊ ሥርዎ መንግስት መሪዎች፡-
ተስፋእየሱስ 1270 አስከ 1285 ዓ.ም ያግባ ጽዮን/ሰለሞን/ ከ1285 አስከ 1294ዓ.ም
ባህር አሰግደ በመቅደም ህዝብ አሰገድ ተከትሎ ጽንፍአርድ/ህዝብ አሰግድ ለአንድ ዓመት ገዛ በመቀጠል ቅድመ አሰገድ ገዛ፡፡ ዠን አሰግድ ከ1294 አስከ 1299 ዓ.ም
ወድም ራ ኦድ ከ1299 አስከ 1314 ዓ.ም አምደጽዮን ከ1314 አስከ 1344 ዓ.ም
ንዋየ ክርስቶስ ከ1344 አስከ 1372 ዓ.ም ንዋየ ማርያም ከ1372 አስከ1382 ዓ.ም
ዳዊት ቀዳማዊ ከከ1382 አስከ 1411 ዓ.ም ቴወድሮስ ቀዳማዊ ከ1411 አስከ 1414ዓ›ም
ይስሀቅ ከ1414 አስከ 1429 ዓ.ም አስክንድር ከ1429 አስከ 1430ዓ.ም
ተክለማርያም ከ1430 አስከ 1433ዓ.ም ሥርዌ እየሱስ 1433 ዓ.ም
አምደየሱስ ከ1433 አስከ 1434 ዓ.ም ዘራያእቆብ ከ1434 አስከ 1468 ዓ.ም
በዕደማርያም ከ1468 አስከ1478 ዓ.ም አስክንድር ከ1478 አስከ 1494 ዓ.ም
አምደጽዮን ዳግማዊ 1494 ዓ.ም ናኦድ ከ1494 አስከ 1508ዓ.ም
ልብነድንግል ከ1508 አስከ 1540 ዓ.ም ገላዊዲዮስ ከ1540 ሰስከ 1559 ዓ.ም
ሚናስ/ወናስሰገድ/ ከ1559 አስከ 1563 ዓ.ም ሰርጸድንግል ከ1563 አስከ 1597 ዓ.ም
ያይቆብ ዳግማዊ ከ1597እከ 1603 ዓ.ም ዘድንግል1603 አስከ1604 ዓ.ም
ያዕቆብ ሀለተኛ ጊዜከ1605 አስከ 1607 ዓ.ም ሱስኒወስ ከ1607 አስከ1632 ዓ.ም
ፋሲለደስ ከ1632 አስከ 1667 ዓ.ም ደጉዮሃንስ ከ1667 አስከ 1682 ዓ.ም
እያሱ ቀዳማዊ ከ1682 አስከ1708 ዓ.ም ተክለሃይማኖት ቀዳማዊ ከ1706 አስከ1708 ዓ.ም
ቲወፍሎስ ከ1708 አስከ 1711ዓ.ም የስጦስ ከ1711 አስከ 1716
ዳዊትሳልሳዊ ከ1716 አስከ 1721 ዓ.ም በካፋ ከ1721 አስከ 1730 ዓ.ም
አዳም ሰገድ /እያሱ/ከ1730 አስከ1755ዓ.ም አዳም ሰገድ ሳልሳዊ ከk1755 አስከ 1769 ዓ.ም
አዳም ሰገድ ዳግማዊ/ዮሀንስ/ 1769 ዓ.ም ተክለሃይማኖትዳግማዊ ከ1769 አስከ 1777 ዓ.ም
ሰለሞን ዳግማዊ ከ1777 አስከ 1779 ዓ.ም ተክለገዮርጊስ ከ1779 አስከ 1784 ዓ.ም
እያሱ ሳልሳዊ ከ1784 አስከ 1788 ዓ.ም በዕደማርያም ከ1788 አስከ1789 ዓ.ም
ህዝቅያስ ከ1789 አስከ1795 ዓ.ም በዕደማርያም ዳግማዊ 1795 ዓ.ም
ሰለሞንሳልሳዊ ከ1796 አስከ 1797 ዓ.ም ዮናስ ከ1797 አስከ 1798 ዓ.ም
ተክለገ‹ዮርጊስ ለ5ኛ ጊዜ በ1799ዓ.ም ሰለሞን ሳልሳዊ ለ2ኛ ጊዜ 1799 ዓ.ም
ድሜትሮስ ከ1799 አስከ 1800 ዓ.ም ተክለጊዮርጊስ ለ6ኛ ጊዜ በ1800 ዓ.ም
ዲሜጥሮስ ለ2ኛ ጊዜ ከ180 አስከ 1801 ዓ.ም እጓለ ጽዮን ከ1801 አስከ 1818 ዓ.ም
ኢዮአስ ዳግማዊ ከ1818 አስከ 1821 ዓ.ም ጊጋር ከ1821 አስከ 1826 ዓ.ም
በዕደማርያም ሳልሳዊ በ1826 ዓ.ም ጊጋር ለ2ኛ ጊዜ ከ1826 አስከ1830 ዓ.ም
እያሱ 4ኛከ 1830 አስከ 1832 ዓ.ም ገብረክርስቶ 1832 ዓ.ም
ሳህለ ድግል ከ1832 አስከ 1840 ዓ.ም ዮሀንስ ሳልሳዊ ከ1841 አስከ 1842 ዓ.ም
ሳህለ ድንግል ለ2ኛገዜከ1842 አስከ1855 ዓ.ም ቴወድሮስ ዳግማዊ ከ1855 አስከ 1868 ዓ.ም
ተክለጊዮርጊስ ዳግማዊ ከ1869 አስከ 1872 ዓ.ም ዮሀንስ 4ኛዉ ከ1872 አስከ 1887 ዓ.ም
ዳግማዊ ምኒልክ ከ1889አስከ 1913 ዓ.ም ልጅ እያሱ ከ1913 አስከ 1916 ዓ.ም
ዘዉዲቱ ንግስተ ነገስት ከ1916 አስከ1930 ዓ.ም ቀዳማዊ ሀይለስለሴ ከ1930 እስከ1974 ዓ.ም( ብላቴን ጌታ ሂሩይ መጽሃፍ ከገጽ 8–45)
መንግስቱ ኃይለማርያም ከ1974 አስከ 1991 ዓ.ም መለስ ዜናዊ ከ1991 እስከ 2012 ዓ.ም
ሀይለማርያም ደሳለኝ ከ2012 አስከ 2018 ዓ.ም ዶ/ር ዓቢይ አህመድ ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ
በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን መንግስሥት ዳማትን ጠቅሰን ወደ አኩሱም አልፈን ዛጉየ ከ1150—1270 ባለዉ 700 ዓመታት ብንመጣ አንድም የዐማራ የዘር ሀረጉን የሚመዝ ስልጣን ላይ የተቀመጠ አናገኝም፡፡ አጼወቹ እራሳቸዉ አንድም ቀን ዐማራ ነን ብለዉ አያዉቁም የራሳቸዉን ማስረጃ እንጥቀስ-(ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ ሥዩመ እግዚአብሄር ንጉሠ-ነገሥት ቀዳማዊ፣ዳግማዊ፣ሳልሳዊ፣ወዘተ ዘኢትዮጵያ)ነዉ የሚሉት፡፡ ሲተነተን አንበሳዉ ከይሁዳ ነገድ መነሻዉን ያደርጋል፡፡ይሁዳ እስራኤልን እንጂ ዐማራዉን አይወክልም፡፡ የመሪዎች መነሻ በአባታቸዉ በኩል የእስራኤል ንጉስ ሰለሞን ከወለደዉ ቀዳማዊ ምኒልክ ነዉ ይላሉ፡፡ዘር የሚጠራዉ በአባት ነዉ የሚሉ መሪዎች መነሻ አባት እስራኤል ነዉ፡፡ ዐማራ ደግሞ
እስራል አይደለም፡፡መሪዎች ቢመቹም ባይመቹም በአባታቸዉ እስራአል ነበሩ፡፡ (ታየ ቦጋለ መራራ እዉነት ገጽ 369)
ከ1270 አስከ1974 ባለዉ ዘመን ዉስጥ ከ1520-1620 የኦሮሞዎች የወረራ ዘመን መሆኑን ታሪክ አስቀምጧል፡፡ታዲያ ዐማራዉ የገዛዉ ከመቸ እስከ መቸ ነበር ገዥ ዐማራዎች አነማን ነበሩ የቅርቦቹን ብንጠቅስ አጼ ተክለጊዮርጊስ ዋግ ናላስታ፣አጼ ዮሀንስ 4ኛዉ ትግራይ፣አጼ ምኒልክ ኦሮሞና ዐማራ፣ ልጅእያሱ መሀመድአሊ ከ8 አንድ ዐማራ፣ ዘዉዲቱ ምኒልክ እሩብ ዐአማራ፣አጼ ኃይለስላሴ መኮነን ኦሮሞ፣መንግስቱ ሃይለማሪያም ኦሮሞ፣መለስ ዜናዊ ትግሬ፣ኃይለማርያም ደሳለኝ ወላይታ እና ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ኦሮሞ ናቸዉ፡፡ዐማራዉ ኢትዮጵያን የመሩትን ሁሉ በኢትዮጵያነታቸዉ አምኖ ይቀበላል፡፡ በባንዳነት ተሰልፈዉ ከወራሪዎች ጋር አገረ የሸጡትን ሕዝብ የበደሉትን በህግ ይጠይቃል አስከ መጨረሻዉ ይታገ ላቸዋል እንጂ የባንዳዎችን ልጆች መስሎ እና ተከትሎ ለወራሪ አገሮች በባንዳነት ተሰልፎ የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር በጎሳ ከፋፍሎ ኢትዮጵያን ለማጥፋት በምንምታምር ዐማራዉ አይሰለፍም፡፡
ትምህርትን በተመለከተ የዘመናዊትምህርት ከተጀመረበት በተለይም ከጣሊያን ወረራ በኋላ ከንጉሡ ከስደት መመለስ ጋር አብሮ ተዳብሎ የመጣዉ የአዉሮፓዊያኑ የካቶሊክ እና የሉትራን መካነ እየሱስ የተባሉ ሀይማኖቶች ነበሩ እነዚህ ሀይማኖቶች በአፍሪካ የቅኝ ግዛት ታሪክ እና የባሪያ የንግድ ታሪክ የሚያሳፍር ታሪክ በተደጋጋሚ የፈጸሙ ናቸዉ፡፡በወለጋ የሉትራን ሀይማኖት በጀርመን እና በኖርዌይ ዲታዎች እና መንግሥታት አመራር ሥር ያለ የፖለቲካ ተወካይ ነዉ፡፡ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡በተለይ ጀርመን ሕዝቡን በጁ ለማድረግ የተጠቀመችበት መንገድ ት/ቤቶችን በማሳፋፋት እና የአስተማረችዉን ትዉልድ በፀረ ኢትዮጵያ ሀሳብ ማጥመቅ ነበር፡፡ ጀርመን ወደ ኢትዮጵያ በአቅኝነት ለመግባት የሞከረችዉ አባ ጅፋርን በመወዳጀት እንደነበር ተመልክቷል፡፡ በሱዳን በኩል በተደጋጋሚ በመጎብኘት የታወቀዉ የጀርመን የታሪክ ጸሀፊ ስለጅማ የንግሥና ሥርዎ መንግሥት ታላቅነት ጽፏል፡፡በዩነቨርሲቲዉ ዉስጥ የተሰባሰቡትን የሉትራን እምነት ተከታይ ተማሪዎች ስለ ኦሮሞ ነፃነት ዋና አቀንቃኝ ሁነዉ ተነሱ ዛሬም ጀርመን እና ኖርዌይ የኦነግ የዉጭ ስንቅ መሰነቂያና የመሰባሰቢያ መድረካቸዉ በመሆን ያገለግላሉ፡ ፡(ተስፋየ መኮነን ትዉልድ እና ቅርሱ መጽሀፍ ገጽ 71 )፡፡
የኦነግ መሪዎች አፍሪካን በመዉረር ላይ እያሉ በኢትዮጵያዊያን አርበኞች ሙሉ ምኞታቸዉ ሳይሳካላቸዉ የቀሩት ምዕራባዊያን አገሮች በጦርነት ሳይሆን በዐማራዉ ላይ ሌሎችን በማዝመት ማጥፋት ይቻላል ብላዉ በአገኙት የጥናት ዉጤታቸዉ መሰረት የተገኙት የጥፋት መሪ እና አቀንቃኝዎች ናቸዉ፡፡ ለጥፋታቸዉ መነሻ አድርገዉ ከሚቀርቧችዉ ቋንቋ፣ትምህርት እና መሬት ናቸዉ፡፡ቋንቋን በተመለከተ የድሮ ፖለቲከኞች የአቀረቡት ምክንያት የኦሮሞን ቃላት በግዕዝ ፊደል መጻፍ አይቻልም የሚል ነዉ ለዚህ ሃሳባቸዉ ሃሰትነት ማስረጃ እጅግ በጣም ብዙ ናቸዉ፡፡ከነዚህም ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸዉ
በደርገ ዘመን በሬሳ የሚባል ጋዜጣ ይታተም እንደነበር፣ከዛሬ 120 ዓመት በፊት ቄስ አናሲሞስ ነሲብ የተባለ ሰዉ ቅዱስ መጽሀፉን ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ዕራይ ዮሀንስ ከትቦበት እንደነበረ፣ከ200 ዓመታት በፊት እንደተጻፈበት የሚያሳየዉ ሰነድ በቀጣፊዉ ጆግራፌ ላጠና ነዉ ብለ በስለላ እና በስርቆት ተሰማርቶ ብርቅየዉን መጽሀፈ ሄኖክን የዞ በኮበለለዉ ጀምስ ብሩስ እጅ የተገኘዉ ሰነድ፣ከ16ኛዉ ክፍለ ዘመን በፊት የተከተባዉ በሀረር የሚገኘዉ ቅዱስ ቁርዓን ፣ከ1845 ዓ.ም ከአጼትዎድሮስ ዘመነ መንግሥት በፊት የመጽሀፍ ቅዱስ ወንጌል በከፊል የተጻፈበት፣በ1967 ዓ.ም ከ20 በላይ በሆኑ ብሔር እና ብሔረሰቦች ቋንቋ የመሬት አዋጅ ፈትፍቶ እና ቁልጭ አድርጉ የተገለጸበት፣ከ30 በላይ ብሔረ ብሔረሰቦች ቋንቋዎች በጥራት እና በብቃት መሰረተ ትምህርት የተሰጠበት፣በሬሳ ታላቁ የአፋን ኦሮሞ ጋዜጣ በበርካታ ቁጥሮች ለዘመናት ሲሰራጭበት የነበረ፣በደርግ ዘመን ከ45 ብሔር ብሔረሰቦች በላይ ቋንቋዎች የተገለጹበት፣በርካታ
የእስልምና ዝክሮች መንዙማዎች የተጻፉበት፣በርካታ የክርስትና መዘምራት በኦሮምኛ እና በሌሎች ቋንቋዎች የተገለጹበት፣ከረጅም ዘመናት በፊት በአፋን ኦሮምኛ የመዝገበ ቃላት የተደራጀበት፣ በዶ/ር አበራ ሞላ እና በፕሮፌሰር ባዩ ይማም በተደረገ ጥናት መረጋገጡ ወዘተ ናቸዉ፡፡
ዘመናዊ ትምህርት የተጀመረዉ በ1898 ዓ.ም በሀረር ከተማ የራስ መኮነን ት/ቤት ነዉ፡፡ በ1900 ዓ.ም ዳግማዊ ምኒልክ ት/ቤት አዲስ አበባ ነዉ፣ በ1917 ዓ.ምተፈሪ መኮነን አዲስ አበባእና በወለጋ የደጃች ገብረእግዚአብሄር ት/ቤት ነዉ፡፡በዓመቱ በ1918 ዓ.ም 23 የወለጋ ልጆች ወደ አዲስ አበባ በመላክ በተፈሪ መኮነን ት /ቤት በአዳሪነት ተምረዋል(መርሴሀዘን ወልደ ቂርቅስ እንደጻፉት)በዘመናዊ ትምህርት የመጀመሪያዎቹ የዉጭሃገር ተማሪዎች ሦስት ሲሆኑ ሁለቱ ኦሮሞዎች ነበሩ እነሱም መላኩ በያን በኋላ ዶ/ርኦሮሞ አና ወርቁ ጉበና ኦሮሞ ሲሆኑ ሦስተኛዉ ባሻህዉረድ ሀብተወልድ ነበር መጀመሪያ ህንድ ሂደዉ አልተስማማነም በሚል ወደ አሜሪካ ሂደዉ 29ኛዉን የአሜሪካን ፕሬዝዳንት ዋረን ሀርዲንግን ተገናኝተዉ ፕሬዝዳንቱ ከተማሩበት ኦሀዮ ማርታ ኮሌጅ እንዲማሩተ ደርጓል፡፡ከ2 ዓመት በኋላ ለትምህርት ከተላኩት 33 ተማሪዎች ዉስጥ አብዛናዎቹ ኦሮሞ ነበሩ ከነዚህ ዉስጥ መሀመድ ማህዲና፣ከሊል ማህዲ፣ወልደኪዳን ቢያን፣ወዳጀ ኢካ፣ዮሀንስ ቦሩ፣ገብረየስ ገቱ፣ገብረማርያም አመንቴ አበራ ደገፋ ይገኙበታል፡፡ት/ቤቶች
ሀረርጌ 214 47 7 ኢሊባቡር 137 14 4 ከፋ 93 11 3 ሲዳሞ 148 31 6 ትግራይ 178 19 7 ወለጋ 463 28 10 ወሎ 158 23 3 በአለፈዉ ሥርአት ያልተማረዉ ኦሮሞ በወለጋ ብቻ የነበረዉ ት/ቤት 463 በኢትዮጵያ በአንደኝነት ደረጃ ነበር በኢትዮጵያ የነበሩት ሁለት ማየት የተሳናቸዉ ት/ቤቶች ደምቢደሎ እና ሰበታ ብቻ ነበሩ ይህን ቁልጭብሎ የሚታይ ሀቅ ነዉ እነጁነዲን በኦሮሞ ትምህርት ተከልክሎ ነበር በማለት መለስን ለማስደሰት ሲል ይናገር የነበረዉ፡፡
መሬትን በአስመለከተ አድማስ በከለለዉ ዘርግቶ ይዞት የነበረዉ ራስ መስፍን ሰለሺ የኦሮሞ ተወላጅ እናባለቤት፣የጃራ መስፍን እናት እና የቄለሙ ደጃዝማች ጆቴ ቱሉ የልጅ ልጅ የሆኑት ወ/ሮ የሽመቤት ጉማ ወለጋዉስጥ ብቻ 500 ጋሻ መሬት ነበራቸዉ፡፡በደርግ መንግስት የመሬት ለአራሹ አዋጅ ሲታወጅ አዋጁን የአወጡት የመሬት ይዞታ ሚኒስቴር ዘገየ አስፋዉ፣ባሮቱምሳ፣ዲማ ነጎ እና ፈቃዱ ዋቅጅራ የኦነግ መስራች ፋኖዎች ነበሩ፡፡ከአሰፈሯቸዉ ነጥቦች ዉስጥ የገጠር መሬት የተባለ ሁሉ የመንግስት ይዞታ እንዲሆን፣ ማንኛዉም ተቋምም ሆነ ግለሰብ መሬትን በግል ንብረትነት መያዝ የማይችል መሆኑን፣ማንኛዉም ሰዉ
ጠቅላይ ግዛት ከ1—6ኛ ክፍል ከ7—8ክፍል ከ9—12 ክፍል አሩሲ 135 19 3 ኤርትራ 428 66 14 ባሌ 83 8 1 ጋም ጎፋ 77 8 3 ጎጃም 135 14 4 ጎንደር 184 21 4
መሬቱን የመሸጥ የመለወጥ የማዉረስ ሆነ በወለድ አገድ ለማስያዝ የማይችል መሆኑን በመደንገግ ለወያኔ ዘመን የመሬት ገፈፋ የአመቻቸዉ ኦነግ ያዘጋጀዉ የመሬት ለአራሹ አዋጅ ነዉ፡፡
ታሪክ የሰዉ ልጅ በአለፈባቸዉ ሥርዓተማህበር ዉስጥ በእየአንዳንዱ ምጣኔ ሀብታዊ፣ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ፣ባህላዊ፣ፖለቲካዊ እና የእመነት አምዶች ዙሪያ የሚያደርጋቸዉ መስተጋብሮች ናቸዉ፡፡ የታሪክ ጥናት ትናንትን የሚመረምረዉ ለዛሬዉ የማይቆረቁር መደላድል ለማመቻቸት፣የትስስር ገመዱን ለመጠበቅ እና የችግሮችን እንቆቅልሽ ለመፍታት ነዉ፡፡በትናንት መስታዉት እነት ዛሬን በጥሩ መሰረት ላይ ማነጽ በእዉነት ለተማረዉ የታሪክ ትምህርት እምብርት ነዉ፡፡፡፡በዚህ እዉነታ ከአመን ከዚህ በላይ በተተረከዉ ትርክት ከአገኘናቸዉ አዉነታዎች ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸዉ፡፡
ኢትዮጵያ ከሌሎች አገሮች ቀድማ በሀለተኛ ደረጃ መገኘቷ፣የኢትዮጵያ ታሪክ ከመካከለኛዉ ምስራቅ አገሮች ቅድሚያ ያለዉ መሆኑን፣የኢትዮጵያ የቋንቋ ቤተሰቦች እና ማህበረሰቦች ባሀዉርታዊ እና ጥንታዊነት በአርኪዮሎጂ እናፓሊዮንቶሎጂ መረጃዎች መረጋገጡ፣ከእስያ ክፍለ አህጉር ወደ ኢትዮጵያ ገቡ የተባሉት የዉጭ አገሮች ሳይሆኑ የኢትዮጵያ ነባር እና ጥንታዊ ህዝቦች መሆናቸዉን፣ የዳማት ፊደል የተገኘዉ በኢትዮጵያ ብቻ መሆኑን የቋንቋ ሳይንስ እና የአርኪዮሎጂ መረጃዎች ማረጋገጣቸዉ፣የኢትዮጵያ ሥልጣኔ ምነጩ፣ መነሻዉ እና ባለቤቱ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸዉ፣የኢትዮጵያ ቋንቋዎች አገር በቀል መሆናቸዉን እና ከዉጭ የመጣ አንድም ቋንቋ አለመኖሩን፣መዕራባዊያን ታሪከን ላለመነጠቅ ሲሉ የታሪክ ምንጭ የሆኑትን አገሮች የግብጽን የኑቢያንእና የኢትዮጵያን ህዝብ ነጭ እንጂ ጥቁር አይደለም ማለታቸዉ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ አዉሮፓዊያን ከጻፉት የእመነት ታሪክ ተላቆ በእዉቀት እና በማስረጃ ተደግፎ እንዲጻፍ ማስፈለጉ፣የኢትዮጵያ መልካ ምድራዊ አቀማመጥ ከብዙ አካባቢዎች ብዙ መዘዝ የሚያመጣ ጂኦፖለቲካዊ አምብርት መሁኑ፣ፖርቹጋሎች ቱርኮች እንግሊዞች ፣ፈረንሳይዎች ጣሊያኖች ጀርመኖች ዘግይተዉ አሜሪካኖች የክልሉ ብቸኛ ገዥ ለመሆን መጣራቸዉን፣በአዉሮፓዊያን የቅርምት ዘመን እንግሊዝ ፈረንሳይ እና ጣሊያን ከግብፅ በስተጀርባ ኢትዮጵያን በተደጋጋሚ መዉረር፣ከ1881 ዓ.ም ጀምሮ ጣሊያን በእንግሊዝ አመካይነት በተደጋጋሚ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት በመክፈትሳይሳካላቸዉ መቅረቱን፣አዉሮፓዊያን በጦርነት አልስካላቸዉ ሲሉ መፈትሄ ፍለጋ በሰላየወቻቸዉ አስጠንተዉ የደረሱበት ድምዳሜ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ዐማራን መጥፋት ነዉ የሚልመሆኑን፣ዐማራን ለማጥፋት በእርዳታ፣በሀይማኖት፣ በጉብኝት፣ በመምሀርነት፣ እየገቡ ሌላዉን ብሔር በሔረስብ በዐማራ ላይ የጥላቻ ዘመቻ እንዲያካሂድ መቀስቀስ፣ ማስተማር፣ መስበክ ለዚህም አመቹ ቦታ ዩነቨርሲቲዉ እንደሆነ ወስነዉ መነሳታቸዉን፣የአዲስ አበባ ዩኘቨርሲቲ በጥቂትብሔርተኞች ትስስር የሚመራ ወሳኝ አካላት ጥቂት የሚሆንበት ኦልጋሪክ መስተዳድር የጎለበተበት መሆኑን፣የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የዐማራዉ የጥላቻ ስብከት የሚፈጸምበት የዐማራ ተማሪ በሚያሳየዉ ትምሀርት አክቲቪቲ የሚባረርበት መሆኑን፣
ከ1520 አስከ 1620 ዓ.ም የኦሮሞ ወረራ በሁሉም ኢትዮጵያ መፈጸሙን፣በኦሮሞ ወረራ ወቅት ሌሎች ጎሳዎች እና ነገዶች ማለቃቸዉ፣መሰደዳቸዉ የተረፉት በሞጋሳ በጉዲፈቻ እና በግዳጅ ማንነታቸዉን ወደ ኦሮሞነት መለወጣቸዉ፣ኦሮሞ በወረራዉ ወቅት ለም መሬቶችን በስፋት መያዙን፣የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር ብዛት መጨመሩን፣የሮማን ካቶሊክ ወደኢትዮጵያ የገባዉ የአረቶዶክስ ሃይማኖት ለማጥፋትመሆኑን፣ የእስፓኝ ካቶሊክ ሚሲዮናዊ ቄስ ፔትሮፓያዝ ከ1564 እስከ1622 ዓ.ም የጎንደር መንግሥታትን በጦር መሳሪያ እርዳታ ታኮ መስበኩ፣በሰበካዉም አጼሱሲኒየስ ለ1300 ዓመታት የኖረዉን የክርስትና ሀይማኖት በአዋጅ ሽሮ የሮማንን ካቶሊክ ክርስትና ማጽደቁን፣በኦሮሞ ወረራከ21 በላይ አካባቢዎች ስማቸዉ የተቀየረ ቦታዎች እና ሕዝባቸዉም ማንነቱን የአጣ መሆኑን፣የኦሮሞ ምሁራን የኦሮሞ ችግር ከዐማራዉ ጋር ተጋብቶ፣ ተዋልዶ፣ ተስማምቶ መኖሩነዉ፡፡ ሰለዚህ የተጋባህ ተፋታ ያልተጋባህ ከዐማራ ጋር እንዳትጋባ እያሉ ወጣቱን ትዉልድ የሚያሰትምሩ እና ትምህርታቸዉን ተቀብለዉ ለሚያሰተጋቡ ወጣቶች
በጭብጨባ የሚያጠናክሩ ምሁር ተብየዎች መኖራቸዉን፣ወያኔዎች እና ኦነጎች የኢትዮጵያ አንድነት ከተጠናከረበት ከምኒልክ ዘመን ጀምሮ ከወራሪ አገሮች ጎን ተሰልፈዉ ኢትዮጵያን በማጥፋት ላይየ ነበሩ እና አሁንም ያሉ መሆናቸዉን፣አጼ ምኒልክ ኢትዮጵያን በተማከለ መንግሥት አቋቁመዉ ለመዕከላዊ መንግሥት ብቻ ግብር እንዲከፍል ማድረጋቸዉን በዚህም ሕዝቡ እና አብዛኛዉ መሪ አምኖ የአሩሲዉ መሪ ብቻ አልገብርም ብሎ ጦርነት በመክፈቱ በራሳቸዉ በኦሮሞዎች እዲገብሩ መደረጋቸዉን ፣አገር ወዳድ የሆኑ ኦሮሞዎች ከሁሉም በላቀ ጀግንነት ምኒልክን አረድተዉ መዋጋታቸዉን፣በኢትዮጵያ ከመጀመሪያዉ ከዳማት መንግሥት ጀምሮ እስከ ዶ/ር አቢይ አህመድ የዐማራን የዘር ሀረግ መዞ ስልጣን ላይ የተቀመጠ አንድም አለመኖሩን፣የኢትዮጵያ ታሪክ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ1013 ዓ.ዓ ከንግስተ ሳባ የንግሥና ዘመን ጀምሮ እስከ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዘመን 2012 ዓ.ም የነበሩ ነገስታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ከንግሥት ሳባ አስከ ባዚን የገዙብዛት 68 የአኩሱም ዘመነ መንግስት ከአብርሀ ወአጽብሀ እስከ ድለነአድ የገዙብዛት 59 የዛጉየሥርዎ መንግስት ከመራ ተክለ ሀይማኖት አስከ ይትባረክ የገዙ ብዛት 16 በሽዋ የማህዙሚ ሥርዎ መንግሰት ከባዲት ማያ እስከ አብደላ ኢብን የገዙ ብዛት 13 ከይኩኖ አምላክ ከተስፋ እየሱስ እከ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የገዙ ብዛት 71 አጠቃላይ ብዛት 227 ነገስታት የአስተዳደሯት አገር መሀኗን ታሪክ ያስረዳል፡፡ለመጥፋት በአፋፍ ላይ ያለችዉን ኢትዮጵያን ማዳን የሚችለዉ ዐማራዉ እራሱን በድርጅት አጠንክሮ ዐማራን መነሻ ኢትዮጵያን መድረሻ በማድረግ ሌሎችን በማሰባሰብ መስራት ሲችል ብቻ ነዉ፡፡ኢትዮጵያን ከጥፋት የሚጠብቃት ዐማራ ብቻ መሆኑን ኢትዮጵያን ለማጥፋት በቅድሚያ ዐማራን ማጥፋት ነዉ ብሎ አቅዶ በመነሳት ዐማራንያጠፋዉ መለስ ዜናዊ ሳይቀር እንዲህ ሲል መስክሯል፡፡ ዐማራ ኢትዮጵያዊነትን ዘልቆ የተዋሀደ እና ከደመነፍሱ ጋር የተሳሰረ ነዉ፡፡ ይህነን ከሕዝቡ ሥነአዕምሮ ነጥሎ ለመጣል በዘር፣በቋንቋ ማደራጀት እና በዚህ ዓላማ የሚመሩ ድርጅቶችን መፍጠር ነዉ፡ ፡በመሆኑም ኢትዮጵያን ለማጥፋት በቅድሚያ ዐማራን ማጥፋት ነዉ፡፡ዐማራ ነን የሚሉትም ሌሎችም በዐማራ ላይ የዘመተ ነዉ ስል የአለፉት የቅርብ እና የሩቅ ጊዜ አጼዎች በሰጡነ ኢትዮጵያ ላይ ነዉ፡፡ ዐማሮች ሲመነጠሩ ሌላዉ ኢትዮጵያዊ የሚቆጣዉ ኢትዮጵያን የማፍረሱ ዓላማ ሲፈጸም ወለል ብሎ ስለታያቸዉ እንጂ ዐማራ ሰለሆኑ እና ለዐማራዉ አድልተዉ እንዳልሆነ ዐማራ ይረዳል፡፡ የኢትዮጵያ ሌላዉ ገጽ ዐማራ እንደሆነ ዐአማራ ከጠፋ ኢትዮጵያ አንደምትጠፋ አበክሮ ለተከታይዎቹ አስተምሯል፡፡ ጽፏል፡፡ ሲሞትም ተናዞአል፡፡
ሮማን ፐርቻስካ በጻፈዉ መጽሃፍ ገጽ ሦስት ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ አንድ ዐማራ የሚባል ነገድ እኛ ምዕራባዊያን በአፍሪካ በምናደርገዉ የመስፋፋት ፖሊሲ ትልቁ እንቅፋት ነዉ፡፡ዐማራ ከተደራጀ እንኳን ለአፍሪካ ለኛም ትልቅ ስጋት ነዉ በማለት ጽፏል፡፡ሩዶልፍ የተባለ ጸሀፊ ዐማራ ለኢትዮጵያ የቆመ ሃይል ነዉ፡፡ዐማራ እንዳይደራጅ ጠበቁት ዐማራ ለጊዜዉ የተሸነፈ መስሎ አንገቱን ቢደፋ ቀን ጠብቆ መነሳቱ አይቀርም የሞተ አማራ አይነሳም ብሎ ማመን እንጂ የተዳከመ ዐማራ አይነሳም ብሎ ማመን ቂልት ነዉ ሲል ዐማራ ለኢትዮጵያ የቆመ ሀይል መሆኑን አረጋግጧል፡፡
የዐማራ ጠላት ማን ነዉ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተሰለፈ ሁሉ የዐማራ ጠላት ነዉ፡፡ የሩቅ ጠላቶች ቱርኮች፣ፖርቹጋሎች፣እንግሊዞች፣ ፈረንሳይዎች ጣሊኖች ጀርመኖች ግብጾች ወዘተ ናቸዉ፡፡ምክንያቱ አፍሪካን ለመዉረር ሲመጡ ኢትዮጵያ በአድዋ ጦርነት ድል ወረራቸዉን በማክሸፏ፣በዚህም ጥቁር ነጭን አያሸንፍም ተብሎ የሚታሰበዉ ዉድቅ ሁኖ ለአፍሪካዊያን የአንገዛምነት ወኔ በማላበሱ፣ የናይጀሪያ መሪ ናሚድ ኢዘአድ ኢትዮጵያ በአለም ገጽ ከጡፉት የጥቁር ግዛቶች የተረፈች ብቸኛ የተስፋ ችቦ ነች፣ የአፍሪካዊያን አባቶች እና አያቶች በዚህ አህጉር አቋቁመዉት ለነበረዉ ሥርዓተ መንግሥት ሀዉልት ናት ብሎ በመናገሩ፣ጆርጅ ኤድመንድ ሄይንስ የተባለ ጥቁር አሜሪካዊ ኩሩ እና ነፃዋ ኢትዮጵያ አፍሪከዊ ደም ላለቸዉ ጥቁሮች የነፃነት የራስ መቻለ ከዘመናዊ ስልጣኔ መልካም መልካሙን የመቅሰም እና የንቃተ ህሊና ምልክት ሁናለች በማለቱ፡፡በ1935ዓ.ም የዐማራዉ ገዥ ኃይለሥላሴ ለጦር አለቆቻቸዉ የአፍሪካ ከፍተኛ
ንጉሥ እኔ ነኝ ለዓለም ጥቁር ሕዝቦች ገና ነፃ ያልወጡትን ጨምሮ ብለዋል፣ለማተን ለተባለዉ ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ በቁርዓን ላይ ነቢዩ መሀመድ እንደ አስቀመጡት ኢትዮጵያዊያን አስተናግደዉናል ብለዋል ፡፡ስለዚህ ሙስሊሞች በፈለግን ጊዜ ሊረዱን ይገባል የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል ወዘተ በማለት፤ ኢትዮጵያ በዐማራዉ አማካኝነት በምዕራባዊያን አልገዛም ብላለች በማለት ሮማን ፐርቻስካ በሪፖርት ማቅረቡ፡፡ከምዕራብ ወደምስራቅ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ለንግድ ዝዉዉር የሚጠቀሙበትን የስዊዝ ካናልን እና አካባቢዉን ለመቆጣጠር እንዳያመቻቸዉ በመሆኑ፣ በግብፅ በኩል ገብቶ አባይን ከምንጩ ለመቆጣጠር በተደረገዉ ተደጋጋሚ ጦርነት በመሸነፋቸዉ፤በዚህ ምክንያት በአደረጉት ጥናት ኢትዮጵያን ለማጥፋት ቅድሚያ ዐማራዉን ማጥፋት ነዉ፡፡ ብለዉ በመወሰናቸዉ ፤ኢትጵያን ለማጥፋት በአስፈፃሚነት ቀጥብለዉ ተሰልፈዋል፡፡
የቅርብ ጠላቶች የኢትዮጵያ ባንዳዎች እና ዝርያቸዉ ናቸዉ፡፡ ምክንያቱ ኢትዮጵያን ለማጥፋት በተደጋጋሚ ለወረሯት አገሮች ሁሉ በባንዳነት ተሰልፈዉ ያገለገሉ ጌቶቻቸዉ ድል ሲመቱ፤ እና እነሱ ያገኙት የነበረዉ ጥቅም በመቋረጡ፡፡ በአደረባቸዉ ብስጭት ጌቶቻቸዉ አጥንተዉ በአገኙት አማራጭ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ቅድሚያ ዐማራን ማጥፋት ብለዉ የወሰኑትን የጌቶቻቸዉን ዉሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ፤ ልዩ ልየ ሥልቶችን በመንደፍ በማቀድ ለዕቅዳቸዉ ማስፈጸሚያና መጠቀሚያቸዉን ገንዘብም ሆነ ልዩልዩ ጥቅማ ጥቅሞችን በማግኘት፤ በባንዳነታቸዉ በፈጻሚነትና በቋሚነት ይሰራሉ፡፡አፈጻጸሙ በኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሰቦች ጭቆና አለ ጨቋኙም ገዥዉ ዐማራ ነዉ በማለት ተማሪን ከተማሪ የመለየት ሥራ ተጀምሮ የሚያልቀዉ በዩንቨርሲቲዉ ነዉ፡፡በዘር በነገድ በመቧደን የኤርትራ፣የትግሬ እና የኦሮሞ ድርጅቶች ጠንክረዉ ኢትዮጵን የማፍረስ ሥራ ሲሰሩ፤ እንዳይነቃባቸዉ ማሳሰቻ መኢሶን፣ ኢጭህአት ኢህአፓን በነሱ መሪነት አደራጅተዉ ሲሰሩ የነቁባቸዉን በጭሆት በሁካታ እያስበረገጉ እንዳይናገር በማድረግ፤ በግቢዉ ዉስጥ በማሰፈራራት እንዲያም ሲል ከትምህርት እያፈናቀሉ በትንንሽ የቡድን ስብሰባዎች ዉሳኔ አብላጫዉን በመግዛት፤አዲስ ገቡን ተማሪ እንዳያደናቅፋቸዉ በ1958 የዩቨርሲቲዉ ተማሪዎች ማህበርብለዉ በአወጡትመመሪያ የ1ኛ ዓመት ተማሪ ደምጽ የሚቆጠረዉ በግማሽ እንደሆነ በመደንገግ፤ አገር ለማፍረስ የሚሰራበት የአዲስ አበባን ዩንቨርሲቲ የአዉሮፓዊያን ጉዳይ አስፈጻሚዎች ቢሮ በማድረግ ነበር፡፡
መፍትሄ የዐማራዉ ችግር የኢትዮጵያ ችግር ነዉ፣የኢትዮጵያ ችግር የዐማራዉ እና የሌሎች ለኢትዮጵያ አንድነት እና ሉዐላዊነት መከበር የቆሙ ነገዶች ችግር ነዉ፡፡ ዐማራዉ ሲጠፋ ኢትዮጵያ ትጠፋለች፡፡ ኢትዮጵያ ስትጠፋ ደግሞ ሁሉምይጠፋሉ፡፡ስለሆነም የዐማራዉ ጠላት የኢትዮጵያ ጠላት እንደሆነ የኢትዮጵያ ጠላትም የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ጠላት መሆኑን ተረድቶ በጠላትነት ተፈርጆ እልቂት እየተፈጸመበት ከአለዉ ዐማራ ጎን መቆም ለኢትዮጵያ መቆም መሆኑን የአንድነት ኃይሉ መረዳት አለበት፡፡ ለዐማራዉ ደህንነት እና አንድነት ቁሜአለሁ የሚሉ ኃይሎች እና ቡድኖች ለኢትዮጵያም የቆሙ መሆኑን ከንድፈ ሀሳብ እስከ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ለሁለተኛ እና ለሦስተኛ ወገን ግልፅ ሁኖ ሊታይ በሚችልበት መልኩ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል፡፡ለዚህም የአንድነት ኃይሉ ማናቸዉንም አግባብነት የአላቸዉን እና ሊያሰባስቡ የሚችሉ የኢኮኖሚ፣የሰዉሀይል፣ የሞራል፣የፖለቲካ እና የድርጅት ግቦችን በማቀነባበር፣ መጠቀም መቻል ነዉ፡፡ ለዚህም ግልፅ እና ወጥ ዓላማ፣የዓላማ ማስፈጸሚያ ፣የዓለም አመለካከት (ፍልስፍና) እሬዮተዓለም እና የግብ ጉዞ አመልካች ዓቢይ እስትራቴጂ ነድፎ መንቀሳቀስ መቻል ይጠበቅበታል፡፡መቼ እና እንዴት የተወሰኑ ግቦችን ማሳካት እንደሚቻል ጠቋሚ ወይም አመለካች የሆኑ ዝርዝር የድርጊት ፕግራም ነድፎ በቁርጠኝነት ወደ ሥራ መግባት ይጠይቃል፡፡ወደ ግብ የሚደረግ ጉዞ በስኬት ለመወጣት ያልታሰቡ ድንገተኛ የሆኑ ክስተቶች በጉዞ ላይ መሰናክል እንዳይፈጥሩ አማራጭ የተግባር ክንዉኖች በተጠና መልኩ መቀመጥ መዘንጋት የለበትም፡፡ ድርጅት ለምንወደዉ ህዝብ ለችግሩ የምንደርስበት መንገድ ነዉ፡፡ሀዝብን ስትወድ ለህዝብ የሚበጅ ነገር ለመስራት መደራጀት ነዉ፡፡ይኸዉም
ችግርን መነሻ አድርጎ ጉድለቶችን እየሞሉ ችግሮችን በአጭር፣ በመካከለኛ፣ በረጂም ጊዜ ለማስወገድ ሁሉም ህዝብ የኛነዉ(የኔነዉየሚለዉ ህገመንግስት እና መሪ ሊኖር ይገባል ብሎ መነሳት፡፡
የቅርብ ጠላቶችን ለማጥቃት በመጀመሪያ የዐማራ ድርጅቶችን ማሰባሰብ፤ ቀጥሎ ኢትየጵያን ከጥፋት ከሚከላከሉት ሃይሎቸ ጋር በመሆን ከባንዳወች ጎራ መለየት፤ የዩንቨርሲቲዉን አወቃቀር እና አሰራር መለወጥ፡፡ ፖለቲከኛ መምህራንን ማስወገድ፡፡ በአገሪቱ ዉስጥ በወያኔ የተፈጠሩትን የስራ ስልት አገር አቀፍ በሆነ አሰራር መለወጥ::የዐማራዉ ትብብር መከተል የአለበት ዐማራነት እና ኢትዮጵያዊነት አንዱ ካላንዱ መኖር የማይችል የአንደ ሳንቲም ሁለት ገጽታ መሆናቸዉን አምኖ ለአንድነታቸዉ ደህንነት መታገልነዉ፡፡
የትግል አቅጣጫዉን ዉስብስብነት በመረዳት በአጭር ጊዜ እና በረጂም ጊዜ ዓልሞ እና አቅዶ አዉቆና አሳዉቆ ለተግባራዊነቱ መሰለፍ፡፡ ዐማራን አስተባብሮ የዐማራን ህልዉና አስከብሮ ከሌሎች ብሄሮችጋር መተባበር፡፡ ዐማራዉን በየደረጃዉ በየዘርፉ ማደራጀት ማገናኘት፡፡ ዐማራዉ ገዥበመሆን ሌሎችን ጨቁኗል የሚባለዉን የሀሰት ፕሮፖጋንዳ አንድም የአማራተወላጅ ገዥ አለመኖሩን ዘራቸዉን በመቁጠር በማስረጃ ማጋለጥ፡፡ በወያኔወች ግዛት በዐማራዉ ላይ የተፈጸመዉን ጉዳት በሚታይ እና በሚሰማ ማስረጃ አጠናቅሮ ለተተኪዉ ትዉልድ ማስተላለፍ፡፡ በዐማራዉ ትዉልድ የአክል ጉድለት የፈጠሩትን አሳዶ በመያዝ ለህግ ማቅረብ፡፡ ከኅብረብሔር ድርጅቶች ጋር መወያየት፡፡ ከሌሎች ጋር በመተባበር ማንኛዉም ሰዉ በዘሩ በሀይማኖቱ በሀብቱ በአመለካከቱ የማይገለልባት አንዲት የታፈረች የተከበረች ዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን መፍጠርን የትግሉ አንኳር መርህ ማድረግ፡፡ የትብብራችን የትስስራችን አትኩረት በመሪዎቸ እና በድርጅቶች ሳይሆን በዓላማ ላይ ብቻ ማድረግ፡፡ የድርጅቱን አራይ፣ተልዕኮ ግብ ግልጽ ማድረግ፡፡ በዐማራዉ ክልል ላይ ያገባኛል የሚሉትን ድረጅቶች ሊገዛና ሊመራ የሚችል ቻርተር ማዘጋጀት፡፡ እራስ ወዳድነትን፣ ሥልጣን ፈላጊነትን፣ የቅንነት ጉድለትን፣ግንፍልተኝነትን፣የኔን ብቻ ስሙ፣ ተከተሉ ማለትን አስወግዶ በሀሳብ በህሊና ትግል ድል መንሳት መቻልን ባህል ማድረግ ነዉ፡፡
የሩቅ ጠላቶቻችን ምእራባዊያን አገሮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋሪ ለነሱ ታዛዥ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ መጫን መሆኑን በወያኔዎች የተሰራዉን አለመርሳት ነዉ፡፡ ምዕራባዊያን የአፍሪካ መሪዎች ሕዝብ እየጨቆኑ ሙሰኛ መሆናቸዉን እየአወቁ እርዳታ የሚሰጡት ሕዝቡ ከነፃነት ይልቅ መመገብን ያስቀድማል በሚል፤ ነፃነት ለማግኘት መድረስ የአለበት የኢኮኖሚ ዕድገት ደረጃ አንዳለዉ እና ከዚያ እስከ ሚደርስ ለሆዳቸዉ ብቻ ነዉ ማሰብ ያለብን በሚል ነዉ፡፡ አዉሮፓዊያን ዓላማቸዉን ለማሳካት የሚጠቀሙበት ዘዴ አገርን እየአደኸዩ ጥቂት ቤተሰብ ማበልጸግ እና ዜጎችን ተስፋ እየመገቡ መግደል፤ ቀስበቀስ አገዛዙ ብቻ ሳይሆን ህዝቡም የምዕራቡን እርዳታ በመተማመን በራሱ መተማመንን እንዲረሳ፣እንዲተዉ ማድረግ፡ ፡ በዕራዳታ መተማመን የአካል ብቻ ሳይሆን የአዕምሮ እና የመንፈስ ሽባ ያደርጋል፡፡በምዕራባዊያን አማካኝነት የሚመጣ መሪ የምዕራባዊያንን ዓላማ ለማሳካት ወዳጅ ወይም ጠላት የአልሆኑትን አገሮች ለረጅም ጊዜ ጠላትነት እየፈጠረ፤ የሚያገኘዉን የዕራዳታ ገንዘብ የሚያገለግለዉ ለልማት ሳይሆን ለጦርነት ነዉ ፡፡ምሳሌ መለስ ዜናዊ
ከአዉሮፓዊያን ወደ ኢትየጶያ የሚገባዉ ሁሉ ለኢትዮጵያ ጥፋት በዐማራ ላይ አትኩሮ ስራ የሚጀምር መሆኑን በንቃት መከታተልን እንደሚሻ አዉቆ ምሁራዊ ስራ መስራት፡፡ለኢትዮጵያ ተብሎ የሚጋፈፍ ብድር በወያኔዎች የተበላዉ እና ወደፊትም በተረኛነት የሚበላዉ ገንዘብ እዳ ከፋይ ኢትዮጵያ ከሚለዉ ስምጋር ለሚቀረዉ ዐማራ እንደሚሆን አርቆ ማሰብ፡፡ትግሬዎች ስልጣን ተቀማን በሚል በሀሰት የተነሳዉ ቀዳማይ ወያኔ ዳግማዊ ወያኔን እነመለስን እንደፈጠረ ሁሉ፤ አነመለስ የኛ ነዉ ብለዉ የያዙትን የዐማራ መሬት አልፎ ስሜን ተራራ የኛ ነዉ ብለዉ፣ ካርታ ሰርተዉ፣ መጽሀፍ ጽፈዉ፣ አንድ ትዉልድ አስተምረዉ፣ ለዓለም አሳዉቀዉ ፣ደብቀዉ ያስቀመጡት ዶክሜንት(መረጃ)የከሀዲዎች ልጆቸ ሳልሳይ፣
ዕራባይ ወያኔ እያሉ የፍልስጤምን እና የእስራኤል ዓይነት ታሪክ እንደሚፈጥሩ አምኖ ለዐማራዉ ትዉልድ በእምድጃ ዙሪያ ሳይቀር እንደ ትግሬዎች ማስተማርነዉ፡፡ሊቀማህ የመጣን ቀማኛ ባላንጋራ ማሸነፍ የምትችለዉ አሱ ተራምዶ የመጣዉን ያህል አንተም ተራምደህ የሱን ስትይዝ ነዉ፡፡ለምሳሌ አንደ ቀማኛ መጥቶ የአንተን ኮት የኔ ነዉ ብሎ ቢይዝብሀ፤ አንተ ማድርግ የአለብህ የሱን ኮት ይዘህ የኔ ነዉ፡፡ ማለት ብቻ ነዉ አንጡራ ንብረትህን ሊያስገኝህ የሚችል ተክክለኛ ዳኛም የምታገኘዉ፡፡ኮትክን ብቻ ጨብጠህ የኔ ነዉ ብትል ንብረትህን ታጣለህ ዳኛዉንም ታስታለህ፡፡የተፈጠረ ነገር ሁሉ እንደሚያድግ ፣አርጅቶም እንደሚሞት፣ አዉቀህ የራስ ፣የጊዜ ፣የቦታ፣ ባለቤት በመሆን ዛሬ በይዞታህ አዉቀህ መስራት ስትችል ነዉ የመማር ምስጢር የሚከሰተዉ፡፡ምሁርነት መለያ ባህሪዉ በራሱ አሳቢ ሆኖ በማድረግ ምጥቁነትን ማግኘት ነዉ፡፡ምሁርነት ማለት ለተወሳሰቡ ችግሮች መፍትሄ ማምጣት ነዉ፡፡ለሚኖርበት ነባራዊ ሁኔታ አመች የሆኑ ቀመሮችን መቀመር ነዉ፡፡ ጠቃሚዉን እና ትክክለኛዉን ነገር መፈለግ ነዉ፡፡ አዉሮፓዊያን ጸሀፊዎች የጻፉት ታሪክ መነሻዉ ሀይማኖት መሆኑን፣ የቤተ መንግሥት እነ የቤተ ክህነት ዜና መዋለ በመሆኑ፣ የታሪክ ዐብዮት በማስነሳት አሁን በምናገኛቸዉ ቅሬት አካሎች ማስረጃነት የሰዉ ልጅ መነሻ /መፈጠሪያ/ ኢትዮጵያ እንደሆነች ቋንቋ እና የቋንቋ ቤተሰቦች መገኛ ኢትዮጵያ የስልጣኔ መነሻ ኢትዮጵያ መሆኗን በተጨባጭ መረጃ መሞገት፡፡ ኢትዮጵያዊያን ከደቡብ ዐረቢያ መጡ ብለዉ የጻፍትን የሀሰት ትርክት በማስረጀዉ ጭብጥነት መከራከር፡፡ በነጭነታቸዉ ቀድመዉ በመናገራቸዉ የሚሉትን የጻፉትን ማመኑን የእምነት ስራ ትተን በእዉቀት ላይ የተመረተ በማስረጃ የተደገፈ ታሪክ መጻፍ መቻል፡፡ አዉሮፓዊያንን በሌላዉ ላይ ተነኮል ማሰብን ትተዉ በተከላካይነት እንዲወጠሩ ማድረግ ፡፡ ለታሪክ አብዮት መነሻ የሚሆኑ የታሪክ መረጃ ዓይነቶች፡-1 የፓሌኦንቶሎጂ ሰባዊ የአጥንት እና የድንጋይ ግኝቶች፣ 2 የሰነድ፣የጽሁፍ፣የቅርስ እና የስእል መረጃዎች 3 የሊንጉዊስቲክስ የሥነ-ልሳን፣የቋንቋ ሳይንስ መረጃ 4 የትዉፊት(የኪነ ቃል፣የአፈታሪክ) መረጃዎች ወዘተ ናቸዉ፡፡
የኢትዮጵያ የርኪዮሎጂ እና የፓሊኦንቶሎጂ መረጃዎች ግኝት
መረጃዉየተገኘበት የመረጃዉ እድሜ በዓመት የግኝት ዘመን
የሀዳር ሰዉ አጽም ከ 4 000 000 በላይ በ1973 ዓ.ም
የኦሞ ሰዉ አጽምና የድንጋይ መሳሪያ ከ2 000 000 በላይ 1967—1968 ዓ.ም
የመል ቁንጥር ሰዉና ድንገይ መሳሪያ ከ1 500 000 በላይ 1965—-1976 ዓ.ም
የላጋ ኦደ ዋሻ እንስሳት ስዕል አራት ዓመት 1970—1978 ዓ.ም
የሻቤ ዋሻ እንስሳት ሥዕል 3 000 ዓመታት በ 1920 ዎቹ
የሽዋየአሩሲ፣የሀረር፣የሲዳማ የብዙ ሺህ ዓመታት በ 1920ዎቹ
የዳማት፣አኩሱም፣የድንጋይ ላይ ጽሁፍ 2500 ዓመታት 1959—-1973 ዓ.ም
ከ522—1981 ዓ.ም በኢትዮጵያ የድጋይ ላይ ጽሁፎችን የአገኙ ምሁራን
የአገኙ ምሁራን የተገኘበት አገር የጽሁፉ ቋንቋ የጽሁፉ ብዛት የግኝቱ ዘመን
ኮስማስ ኢትዮጵያ ጂር 1 522 ዓ.ም
ሰሀዊንፉይዝ “ ጂር 13 1894 ዓ.ም
ክሮሲኒ “ ሳዳ 7 1897—1905
ኢሊትማን “ ጂርሳዳ 97 1906 ዓ.ም
ፋሪቤኒ “ ጂር 8 1905 ዓ.ም
ፍራቺኒ “ ሳዳ 32 1953—56ዓ.ም
ዲሬዌስ “ ሳግ 105 1955ዓ.ም
ሼኒደር “ ሳዳ 3 1970 ዓ.ም
አርቻኮሎጂ “ ጂኢ ሳዳ 160 1955—81ዓ.ም
25 አዘርስ “ ሳጌግር 51 1804—1981 ዓ.ም
ከ 1893 እስከ 1981 የኢትዯዽያ የድንጋይ ላይ ጽኁፎችን የተረጎሙ ምሁራን
ኢሊትማን 105 ጽሁፎችን አግሬዌስ 103 ጽሁፎችን ሬስቻኔደር 38 ጽሁፎችን
ድሬዊስ እና ሸኒደር 51 ጽሁፎችን ክሮሲኒ 9 ጽሁፎችን 10 ሌሎች 78 ጥሁፎችን
የኢትዮጵያ የቋንቋ ቤተሰቦች እና ማኅበረሰቦች ዝርዝር
ኩሻዊ የቋንቋ ቤተሰብ ኦሞዊ የቋንቋ ቤተስብ ሴማዊ የቋንቋቤተሰብ ናይሎቲክ የቋንቋ ቤተሰብ እናማህበረሰቦች እና ማህበረሰቦች እና ማህበረሰቦች እና ማህበረሰቦች ቤጃ፣ ቢለን፣ አገዉ ወይጦ አሪ፣ ዑመር፣ ቦና፣ ማሌ ግዕዝ፣ ትግሬ፣ ትግረ ሙዥንገር፣ሙርሌ ፈላሻ፣ሱማሌ፣ረንዳል ዘይሌ፣ቡላ፣አይዳ፣ ዶርዜ አማራ፣አርጎባ፣ጋፋት ሙርሲ፣ከዋንጉ፣ቦዲ ጋቶ፣አርቦሬ፣ማጎ፣ጎዶ ጎፋ፣ጋሞ፣ማሎ ሀረሬ፣ጉራጌ ትሻና፣ሱሪ፣ባሌ፣ቡሩኑ ዋርዚ፣ገዋዳ፣ጸማይ ሜራ፣ ኮንታ፣ኩሉ ሙሶቃን፣ስልጤ ያንጋቶም፣በርታ፣ኮማ ብይላ፣ኮንሶ፣ኦሮሞ ወላይታ፣ዲማ፣ናኦ ማህበረሰቦች፣ምሁር ኑዌሮ፣አኙዋክ ዳላንች/ገለብ/፣አፋር ዳዉሮ፣ቦሽ፣የም፣ዳዚ አነሞር፣ቸሀ፣ጌቶ፣እዥ ጃብላዊ፣ናራ፣ጉምዝ፣ ኩንማ፣ፉዳሽ ሳሆ፣ሲዳሞ፣ከምባታ ባስኬቶ፣ሻኮማ፣ከፋ እንዲጋኝ፣ወሰኔ፣ኢነር ኩናማ፣ፋዲሽ ሀድያ፣ጠባሮ፣አላባ ሸክቾ/ሞቻ/አገፊሎ አዞርነት በርበራ፣ዝዋይ ሰዶ ቀበና፣ማረቆ፣ጌዲኦ ሽናሻ፣ከራ፣ዘርጉላ ቡርጂ፣ትግረ፣ወርጂ ጋንዲላ፣ጊዲቾ፣ ቃጫማ
ምንጭ የኢትዮጵያ የመከራ ሥርዓት እና የኤርትራ ጥያቄ 1985 ገጽ 24 ዶ/ርላጲሶ ጌድሌቦ
የነገዶች ስብጥር በመኖረያ ክልል በኦሮሞ ዉስጥ የሚኖሩ፡
-አማራ 9.1 ፣ጉራጌ 0.98
ሱማሌ የሚኖሩ፡- አማራ 0፣69፣ኦሮሞ 2.25
በትግሬ የሚኖሩ፡-አማራ 2.6፣ኦሮሞ 1.53 ፣አገዉ0.17 ፣አፋር 0.29
በአማራ የሚኖሩ፡-ኦሮሞ 2.62፣አገዉ 3.46፣ ቅማንት 1
ሀረርየሚኖሩ፡-አማራ32.6፣ኦሮሞ 52.3፣ጉራጌ 4.34፣ትግሬ 1.53
ቤንሻንጉል የሚኖሩ፡-አማራ 22፣ኦሮሞ 13፣አገዉ 4.22፣
በጋምቤላ የሚኖሩ፡-አማራ 7.14 ፣ኦሮሞ 4.83፣ትግሬ1.32
በአፋር የሚኖሩ፡-አማረ 5.22፣ኦሮሞ 0.8፣ትግሬ 0.8፣ወላይታ 5
በደቡብ የሚኖሩ፡-አማረ 4.10፣ጉራጌ 15፣ወላይታ 10.59
የአማራዉ ሐዝብ በኢትዮጵያ ዉስጥ እንዴት እና ምን ያህል እንደሚኖር የቀረበዉ ማስረጃ ያስረዳል፡፡
በኢትዮጵያ የአራት ጊዜ የሕዝብ ቆጠራ በዝርዝር ሲታይ የሌላዉ ነገድ ሕዝብ እየጨመረ ሲሄድ የአማራዉ ግን እየቀነሰ እነደሚሄድ የቆጠራዉ ዉጤት ያሳያል፡፡
በ1976 ዓ.ም በተካሄደዉ ቆጠራ አማራ 12055250 ኦሮሞ 12387664
በ1984 ዓ.ም በተደረገዉ ቆጠራ አማራ 12055250 ኦሮሞ 13027875 ትግሬ 4249697
በ1987 ዓ.ም በተደረገዉ ቆጠራ አማራ 16013625 ኦሮሞ 16968188
በ2000 ዓ.ም በተደረገዉ ቆጠራ አማራ 19878199 ኦሮሞ 25363756
ከዚህ ላይየሚያሳየዉ በ2000 ቆጠራ አማራዉ ከ16 ሚሊዮ 3 ሚሊዮ በመጨመር 19ሚሊዮን ሲደርስ ኦሮሞዉ ደግሞ ከ16ሚሊዮን 9 ሚሊዮን በመጨመር 25 ሚሊዮን መድረሰኑን ነዉ፡፡የዐማራዉ ሕዝብ የጠፋዉን ቁጥር አሟልተዉ ባይናገሩም በአገሪቱ የህዝብ ተወካይዎች ምክርቤት ስብሰባ ላይ 2.5ሚሊዮን አማራ ስልታዊ በሆነ መንገድ እንደጠፋ የህዝብ ቆጠራ ባለስልጣን አጠንክረዉ ሪፖርት አድርገዋል፡፡የዐማራ ምሁራን እና ወጣቶች ልብ ልንለዉ የሚገባን የዐማራ ችግር ዉስብስብ እና ሥር-የሰደደ ለመፍታት ጊዜን፣ መተባበርን፣ ለዚህም ያለመሰልቸት መስራትን የሚጠይቅ መሆኑን አዉቆ መሰለፍን ነዉ፡፡ የዐማራ ችግር ሊፈታ የሚችለዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት ሲሆን ብቻ መሆኑን አዉቆ፤ ለተግባራዊነቱ መነሻ አማራን መድረሻ ኢትዮጵያን አድርጉ ለዉጤት መስራት ሲቻል ነዉ፡፡የሰዉ ልጅ መንፈሳዊ ደስታዉን የሚጎናጸፈዉ በግዴታ በሚያገኘዉ ገቢብቻ ሳይሆን መንፈሱን የሚያድስለት ነገር የተጎናጸፈ እንደሆነ ብቻ መሆኑን አዉቆ ከህሊና ሽያጭ ነፃ ሆኖ መስራት ነዉ፡፡ምሁር ማለት አንድን አስተሳሰብ አንብቦ እንደሃይማኖት ቀኖና እንደወረደ ማስተጋባት አለመሆኑን አዉቆ ለተወሳሰቡ ችግሮች መፍትሄ ማምጣት መቻል ነዉ፡፡
ዕድገትእና ልቅና የሚገኘዉ ከማን አንሸ በሚል በደራ በዉድድር ለአብላጫ ዉጤት መስራት ሲቻል መሆኑን አዉቆ መስራት ነዉ፡፡ ሀ እና ለ ገበሬዎች ናቸዉ ሀ በግብርናዉ ሰነፍ ነዉ ግብርናን ሙያ አሟልቶ አይሰራም ታዲያ ከሰኔ ጀምሮ ከ ለ ሲችል እየሸመተ ሳይችል እየተበደረ ይበላል፡፡ገበረዉ ለ ግን ጎበዝ ገበሬ በመሆኑ ከራሱ አልፎ ለሌላዉ ያቀናል፡፡
ይህ ሂደት ባለማቋረጡ ገበሬዉ ሀ በስምብቻ እኩል መጠራቱ ተሰማዉ እና እንዲህ ሲል አቅራራ ታርሶም ተሸመቶም ይበላል እንጀራ እንደምነህ ጥቃት የሞት ባል እንጀራ አለ፡፡የአማራ ምሁራን ከትምህርት ቤት አስከ እርጅ ዘመኑ አብረዉት በተማሩ እየተጠቃ ያስተማረዉን ሕዝብ እያስጠቃ በመኖሩ ምን አስቦ ይሆን? የአማራዉ ነገር ገልቱ ባል የአላት ሴት ለሌላዉ ሚስት ትሆናለች የተባለዉ ነገር ደርሶበት ሀግ ባይ አጥቶ በዓለም ላይ የሰዉ ልጅ የሚደርሱበት ግፎች ሁሉ ያለወሰን እየተፈጸሙበት መሆኑ ዐማራ ነኝ የሚል ሁሉ በይበልጥም ተረካቢዉ ወጣት ሊያስብበትይገባል፡፡