በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ከ24 ሺህ አለፉ!
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 11,881 የላብራቶሪ ምርመራ 584 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ20 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 285 ሰዎች አገግመዋል።
በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 24,175 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 440 ደርሷል ፤ እንዲሁም አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 10,696 ደርሰዋል።

