August 26, 2020 – Konjit Sitotaw
በኢትዮጵያ ከኮቪድ-19 ያገገሙ ሰዎች ከ16 ሺህ አለፉ!
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 18,724 የላብራቶሪ ምርመራ 1,533 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ16 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 515 ሰዎች አገግመዋል።
በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 45,221 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 725 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 16,311 ደርሷል።
