29 ነሐሴ 2020

በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ መካከል ባለፉት ሁለት ሳምንታት ሲካሄድ በነበረው ድርድር ላይ የተወሰነ ውጤት መታየቱን የኢትዮጵያ ውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ገለጹ።
ሚኒስትሩ ስለሺ በቀለ (ዶ/ር) በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ላይ እንዳሉት ምንም እንኳን በድርድሩ ውጤቶች እየታዩ ቢሆንም የሚጠበቀውን ረቂቅ የስምምነት ሰነድ ለማቅረብ ፍጻሜ ላይ አልደረሰም ብለዋል።
Negotiation on #GERD during the last two weeks made some progress, not yet completed to submit the
expected draft agreement. We expect to reconvene on 14th September 2020
https://facebook.com/1417252521911055/posts/2399381433698154/…2:28 AM · Aug 29, 2020
290 84 people are Tweeting about this
በተጨማሪም የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው የሦስቱ አገራት የውሃ ጉዳይ ሚኒስትሮች ትናንት አርብ ውይይት መካሄዱንና ባለፉት ቀናት በባለሙያዎች መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር ውጤት ሪፖርት መቅረቡን ገልጿል።
መግለጫው የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብጽ ባለሙያዎች ከነሐሴ 15/2012 ዓ.ም ጀምሮ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አሞላልና የውሃ አለቃቀቅ ደንብ ላይ ድርድር ሲያካሂዱ እንደነበር አመልክቶ፤ የዚሁ ውጤት ለአገራቱ ሚኒስትሮቹ ቀርቧል ብሏል።
- “አሁን የሚያጣላው የግድቡ ውሃ ሙሌት ሳይሆን ከተሞላ በኋላ የሚለቀቀው ውሃ ነው”
- የህዳሴ ግድብን ተፈጥሯዊ የውሃ ሙሌት ሂደትን ማስቆም ይቻላል?
- ኢትዮጵያውያን ጮቤ ሲረግጡ ግብፅን ያስከፋው የህዳሴ ግድብ ሙሌት
በሚኒስትሮቹ ስብሰባ ላይም የደቡብ አፍሪካ፣ የአውሮፓ ሕብረትና የአሜሪካ ተወካዮች ታዛቢ ሆነው የተገኙ ሲሆን የአፍሪካ ሕብረት የወከላቸው ባለሙያዎችም እንደነበሩ ተጠቅሷል።
በአገራቱ መካከል እየተካሄደ ያለውን ድርድር ቀጣይ ሂደት በተመለከተም ለደቡብ አፍሪካ ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር እንዲሁም ለአፍሪካ ሕብረት የአስፈጻሚ ምክር ቤት ሊቀ መንበር በደብዳቤ ለማሳወቅ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የዚህ የሦስቱ አገራት ድርድር ሂደት ከሱዳን በኩል የሚሰጥ ማረጋገጫን መሰረት በማድረግ መስከረም 04/2012 ዓ.ም እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ኢትዮጵያ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በቢሊየን ዶላሮች አውጥታ እየገነባችው ባለው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሦስቱ አገራት መካከል ሲካሄድ የነበረው ድርድር በተለያዩ ጊዜያት ለመካሄድ የቻለ ቢሆንም ያለመቋጫ ሲቋረጥ መቆየቱ ይታወሳል።
በተለይ በግድቡ የውሃ አሞላልና አጠቃላይ የሥራ ሂደትን በተመለከተ አገራቱ ለመስማማት ተቸግረው የቆዩ ሲሆን በተለይ ኢትዮጵያ በዚህ ዓመት የግድቡን የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት ለመጀመር የነበራትን ዕቅድ ካሳወቀች በኋላ ለመስማማት አዳጋች ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር።
ነገር ግን ኢትዮጵያ በነበረው ከፍተኛ የክረምት የዝናብ መጠን ታግዛ የመጀመሪያውን ዙር የውሃ ሙሌት ዕቅዷን ማሳካቷን ካሳወቀች በኋላ በቀሪ ጉዳዮች ላይ ድርድሩ ቀጥሏል።