September 8, 2020 – Konjit Sitotaw
በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች ከ60 ሺህ አለፉ!
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 14,815 የላብራቶሪ ምርመራ 1,136 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ16 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 888 ሰዎች አገግመዋል።
በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 60,784 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 949 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 22,677 ደርሷል።

