September 12, 2020 – Konjit Sitotaw 

አምባሳደር ኸርማን ኮህን አሜሪካ ለኢትዮጵያ ከምትሰጠው ድጋፍ ውስጥ ከፊሉን ለመቁረጥ መወሰኗን ተችተዋል!

እ.አ.አ ከ1989 እስከ 1991 የአሜሪካ አፍሪካ ጉዳዮች ሀላፊ የነበሩት ኮህን ድርጊቱ “ኢትዮጵያ በህዳሴ ግድብ ዙርያ የግብፅን አቋም እንድትቀበል ለማድረግ ያሰበ ነው፣ ይህም ስሜት የማይሰጥ ነው” ብለዋል።


Herman J. Cohen

@CohenOnAfrica

U.S. suspension of economic development assistance to put pressure on #Ethiopia to accept Egypt’s position in the Renaissance Dam negotiations makes absolutely no sense. Only result is that the U.S. ceases to be considered an impartial mediator, and Ethiopian position hardens.

1:38 PM · Sep 11, 2020 ·Twitter for iPhone

77 Retweets 15 Quote Tweets 299 Likes

ዲፕሎማቱ አክለውም ይህ የአሜሪካ አካሄድ ከወገኝትነት የፀዳ ሸምጋይ መሆኗን ጥያቄ ውስጥ የሚከት እንዲሁም ኢትዮጵያ በአቋሟ ግትር እንድትሆን ያደርጋል ብለዋል።

ከዚህ በፊትም አሜሪካዊው የመብት ተሟጋች ጄሲ ጃክሰን እንዲሁም ስድስት የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት የአሜሪካንን ውሳኔ በመቃወም ደብዳቤ ለስቴት ዲፓርትመንት ፅፈዋል።