ብሄራዊመግባባትናእርቅ ለኢትዮጵያ: ጥናታዊጽሁፍ (በተክሉአባተ)
በአገራችን ኢትዮጵያ ያለውን ብሄር ገነን ሥርዓት በእውነተኛ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር ለመተካት ኢትዮጵያውያን (የሌላ አገር ዜግነት ያላቸውን ትውልደ ኢትዮጵያውያንንም ማለቴ ነው) የተለያዩ መንገዶችንና ዘዴዎችን በመጠቀም እየታገሉ ይገኛሉ:: በአገር ቤት ያሉ ወደ 100 የሚጠጉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በይፋ ሰላማዊ የትግል ስልት ይከተላሉ ቀላል የማይባል ህዝብም በሰላማዊ መንገድ መታገል እንደሚበጅ ያምናል:: በጣት የሚቆጠሩ ድርጅቶች ደግሞ እሾህን በእሾህ እንዲሉ መሳርያ አንስተው ወደበረሃ ገብተዋል:: እንደ ግንቦት 7 ያሉት ደግሞ ሁሉንም አይነት የትግል ስልት መጠቀም አዋጭ እንደሆነ ያምናሉ:: በአንድም በሌላም መንገድ ስለነዚህ የትግል ስልቶች አንጻራዊ አዋጭነትና አስፈላጊነት ውይይቶች ሲደረጉ ነበር:: ነገር ግን የትኛው የትግል ስልት ትክክለኛ ለውጥ ለማምጣት አስተማማኝ እንደሆነ መደምደም የሚቻል አይመስልም:: ለዚህም ይመስላል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማኅበራዊ ሚዲያዎችና በድረ ገጾች የሚደረጉ ውይይቶችና የሚለቀቁ መጣጥፎች ይህን ጉዳይ በቀጥታ የማያነሱት::
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በርከት ያሉ ውይይቶችና መጣጥፎች እያተኮሩበት የመጣው ጉዳይ ትንሽ የተለዬ ይመስላል:: ብሄራዊ መግባባትና እርቅ ማድረግ ለአገራችን ሰላማዊና ዘለቄታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚችል እየተነገረ ነው:: ብሄራዊ መግባባትና እርቅ ማድረግ ከባህላችን ጋር አብሮ ከመሄዱም በላይ እጅግ አስፈላጊና ወቅታዊም እንደሆነ የሚሞግቱ አሉ:: በአንጻሩ ደግሞ ብሄራዊ እርቅ ፈጽሞ የማይሰራ ከመሆኑም በላይ የህግንና ፍትህን መርሆች የሚቃወም እንደሆነ የሚያስጠነቅቁም አሉ:: አንዳንዶች ደግሞ ስለብሄራዊ መግባባትና እርቅ ማውራትና መወያየት የዋህነት አላዋቂነት ሃይማኖታዊነት እንደሆነ በድፍረት ይናገራሉ:: ሌሎች ደግሞ ሃሳቡ መንግስትና ባለሥልጣናቱን ለመታደግ የታሰበ የቆረጣ ስልት እንደሆ ይጠቁማሉ::
ዳሩ ግን ብሄራዊ ኢትዮጵያዊ መግባባትና እርቅን በተመለከተ ጠቅለል ያለ የዳሰሳ ጥናት እስካሁን አልቀረበም:: ጉዳዩን በተመለከተ የሚደረጉት የተናጥል ውይይቶችና የተጻፉት መጣጥፎች የተሟላ ሃሳብ ለማግኘት አያስችሉም:: እንዲያውም በጉዳዩ ላይ ምን ያህል እንደተጻፈና ምን ምን ዝርዝር ሃሳቦች እንደተነሱ አይታወቅም:: ይህም ብሄራዊ መግባባትና እርቅ በይፋ እንደ አንድ የትግል ስልት እንዳይቆጠርና በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ዳብሮ ሥራ ላይ እንዳይውል ተጽእኖ አሳድሯል:: ይህን ችግር ለመቅረፍ የዳሰሳ ጥናት አስፈላጊ ሆኗል:: የዚህ ጥናታዊ ጽሁፍ ዓላማ ጉዳዩን በተመለከተ የተጻፉትን መሠረት በማድረግ አጠቃላይ ግንዛቤ እንዲኖርና በርዕሱ ላይ ውይይት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማነሳሳት ነው::
የጥናቱዓላማ የዚህ ጥናት ዋና ዋና ዓላማዎች ቀጥለው የተዘረዘሩት ናቸው::
- እስካሁን ድረስ ስለብሄራዊ (ኢትዮጵያዊ) መግባባትና እርቅ በጽንሰ ሃሳብ ደረጃ ምን እንደተጻፈ መመርመር
- ብሄራዊ መግባባትና እርቅን በተመለከተ በሚገባ ያልተብራሩ ሃሳቦችን ለይቶ ማውጣት
- ብሄራዊ መግባባትና እርቅን በተመለከተ ወደፊት በጽንሰ ሃሳብና በተግባር ደረጃ ምን መደረግ እንዳለበት መጠቆም
የጥናቱዘዴና የመረጃ ምንጮች
በእርግጥበድረገጾችበፌስቡክበፓልቶክክፍሎችእንዲሁምበቴሌቪዥንናበሬዲዮፕሮግራሞችጉዳዩን (ብሄራዊመግባባትናእርቅን)የተመለከቱውይይቶችተካሂደውይሆናል::ለዚህጥናትእነዚህንሁሉየመረጃምንጮችማካተቱጊዜወሳጅመሆኑ ታምኖበታል::በመሆኑምከላይየተዘረዘሩትንየጥናቱንዓላማዎችለማሳካትበዋናዋናድረገጾችየታተሙመጣጥፎችንመመልከትጠቃሚናጊዜቆጣቢሆኖተገኝቷል::አንድምየተቀናጀጽሁፍበድረገጾችማውጣትየተለመደነውና:: በመሆኑምይህጥናትአራትዋናዋናድረገጾችንበመረጃምንጭነትተጠቅሟል::እነሱም ECADF Ethiomedia Ethiopian Review እና Zehabesha ናቸው::እነዚህድረገጾችበኢትዮጵያዊያንዘንድበደንብየሚታወቁናፖለቲካዊማኅበራውባህላዊሃይማኖታዊምጣኔሃብታዊናሌሎችንምጉዳዮችያካተቱበርካታናጠቃሚጽሁፎችየሚታተሙባቸውናቸው::በአጠቃላይሲታይእነዚህድረገጾችስለብሄራዊመግባባትናእርቅበቂመጣጥፎችን እንደሚያትሙይገመታል:: በተመረጡት አራት ድረ ገጾችም የተጻፈውን ሁሉ አንድ በአንድ መፈተሽ አሰልቺና ጊዜ ወሳጅ ከመሆኑም በላይ አላስፈላጊም ነው:: በመሆኑም የእያንዳንዱን ድረ ገጽ የመፈለጊያ ሳጥን Search box በመጠቀም በጉዳዩ ላይ የተጻፉትን መጣጥፎች በቀላሉ ማግኘት ይቻላል:: ቀጥለው የተዘረዘሩትን የአማርኛና የእንግሊዝኛ የመፈለጊያ ቃላት ወይም ቁልፎች keywords በመጠቀም አራቱም ድረ ገጾች ተፈትሸዋል::
- National dialogue
- National consensus
- National reconciliation
- ብሄራዊውይይት
- ብሄራዊ መግባባት
- ብሄራዊ እርቅ
በሌሎችድረገጾችጉዳዩንበተመለተመጣጥፎችታትመውስለሚሆን Googleንበመጠቀምተጨማሪ ፍለጋተካሂዷል::ይህንምለማድረግከላይየተዘረዘሩትንየአማርኛናየእንግሊዝኛ የመፈለጊያቃላትንተጠቅሜአለሁ::በአጠቃላይሲታይአራቱድረገጾችበርካታበብሄራዊመግባባትናእርቅላይየተጻፉትንይዘውተገኝተዋል::ዳሩግንበፍለጋውያልተገኙጥቂትመጣጥፎችሊኖሩይችሉይሆናል::የጥናቱ ዋና ዓላማ ስንት እንደታተመ መቁጠር ሳይሆን ምን እንደተባለ መመርመር ስለሆነ ይህ ብዙም አያሳስብም:: ለአንባቢግልጽመሆንያለበትሌላ ጉዳይቢኖርይህጥናታዊጽሁፍየሚያተኩረውየድኅረ 97 ምርጫጊዜንነው::ይህጥናትምርጫውንተከትሎየነበሩትንየእርቅሙከራዎችአያጠቃልልም:: ምንም እንኳን ከዚህ ውጭ የጊዜ ገደብ ባይደረግም በርዕሱ ላይ የተጻፉት ጽሁፎች ለንባብ የበቁት ከ2010 ጀምሮ መሆኑን ግንዛቤ ወስጃለሁ:: የጥናቱ ዋና ዋና ግኝቶች ቀጥለው ቀርበዋል::
የጥናቱግኝቶች
በአጠቃላይሲታይ ብሄራዊመግባባትናእርቅንበተመለከተ 18 ጽሁፎችከ2010 እስከ 2014 ታትመዋል::ከዚህ ውስጥ ግማሽያህሉበ2014 ብቻ የታተሙናቸው::አብዛኞቹ (14ቱ)በ2013 እናበ2014 የተጻፉናቸው::ሰባቱበአማርኛሲጻፉቀሪዎቹ 11ዱደግሞበእንግሊዝኛተጽፈዋል::የ16ቱመጣጥፎችአርእስትናሙሉይዘታቸውብሄራዊመግባባትናእርቅሲሆንቀሪዎቹሁለቱየተጻፉትግንበሌላርዕሰጉዳይላይነው::ቢሆንምግንብሄራዊመግባባትናእርቅከተነሱትአበይትጉዳዮችውስጥይጠቀሳል::አብዛኞቹ መጣጥፎችን ያቀረቡት ብዙውን ጊዜ በተለያዪ ሚዲያዎች የሚታወቁ ኢትዮጵያውያን ፕሮፈሰሮች ወይም ዶክተሮች ናቸው:: ሁሉምጽሁፎችከዚህጽሁፍመጨረሻላይበጸሃፍትስምበታተሙበትዓመትበርዕሳቸውናጽሁፎችበታተሙባቸውድረገጾችተዘርዝረውይገኛሉአንባቢያን ጸሃፍትን በቀላሉ ይለዩአቸው ወይም ያውቋቸው ዘንድ ሙሉ ስማቸውን በቅንፍ ውስጥ ጠቅሻለሁ:: አንድጽሁፍበተለያዩ ድረገጾችታትሞቢገኝምይህጥናታዊ ጽሁፍግንመጀመሪያየተገኘበትንድረገጽብቻይጠቅሳል::
ምንምእንኳንሁሉምጽሁፎችብሄራዊውይይትመግባባትናእርቅዋናጉዳያቸውቢሆንምበዝርዝርያተኮሩባቸውጉዳዮችእንዲሁምየሰጧቸውየመፍትሄሃሳቦችግን የተለያዩናቸው::በአጠቃላይ ሲታይ ግንየሚከተሉትጉዳዮችበተለያዩጽሁፎችተዳሰዋል::
- የብሄራዊእርቅጥቅምና አስፈላጊነት
- እርቅየሚያስፈልጋቸውአካላት
- እርቁንማንማስተባበርወይም መጀመር እንዳለበት
- እርቁእንዴትሊካሄድእንደሚችል
- ብሄራዊእርቅናፍትህ እንዴት ሊታዩ እንደሚገባ
እነዚህንጉዳዮችበተመለከተየተገኙት 18ቱመጣጥፎችምንእንዳስቀመጡቀጥሎ በአጭሩቀርቧል:: በቅንፍ የተመለከቱት የጸሃፍት ስምና መጣጥፎች የታተሙበት ዓመታት ናቸው:: ይህ ጽሁፍ የሚያተኩረው በዋናና ጠቅላላ ሃሳቦች ዙሪያ ስለሆነ ዝርዝር ጉዳዮችን ለመረዳት በአባሪ መልክ የተያያዙትን 18ቱን ጽሁፎች ማንበብ ይጠቅማል:: እንደገና የማሳስበው ጉዳይ ቢኖር 18ቱም ጽሁፎች ሁሉንም ከላይ የተዘረዘሩትን ንዑስ ጉዳዮች እንዳላተቱ ነው::
የብሄራዊ እርቅ አስፈላጊነትና ጥቅም
ሁሉም ጽሁፎች ብሄራዊ መግባባትና እርቅ እጅግ ተፈላጊ የሆኑ ማኅበራዊ እሴቶችን ለመመስረትና ለማጽናት ወሳኝ እንደሆነ ያስገነዝባሉ:: እንዲሁም ከሌሎች የትግል ስልቶች አግባብነትና አተገባበር ጋር ብሄራዊ እርቅን ያወዳድራሉ ያነጻጽራሉ:: አብዛኞቹ ጽሁፎች ብሄራዊ እርቅ የሚያስፈልገው ኢትዮጵያ ያለችበት ዘርፈ ብዙ ችግር ተባብሶ ወደ ከባድ ቀውስ እንዳትገባ ስለሚያደርግ እንደሆነ ያትታሉ:: ያሉትን ችግሮች በህዝባዊ አመጽም ሆነ በጦርነት ለመፍታት አስቸጋሪ ከመሆኑም በላይ ተያይዞ ሊመጣ የሚችለው ቀውስ በቶሎ ማቆሚያ ሊኖረው እንደማይችል የብዙ አገሮችን ተሞክሮ በማንሳት ብዙዎች ያስጠነቅቃሉ:: ለምሳሌ ያህል ጥቂት ስለብሄራዊ እርቅ ጥቅም ወይም አስፈላጊነት የተሰጡት ማሳመኛዎች ቀጥለው ቀርበዋል::
- ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በምርጫካልሆነበጦርነትምካልተቻለህዝባዊአመጽም አደጋ ካለው ብሄራዊ የእርቅ መንግስት ከመመስረት ውጭ ሌላ ምን አማራጭ የለም (መሳይ ከበደ 2013/2014)
- የመንግስት ባለሥልጣናት ሳይቀሩ ስለሚፈልጉ ብሄራዊ እርቅን ለመተግበር የማይቻል አይደለም (ተጋ 2013)
- በቋንቋ በዘር በሃይማኖት በፖለቲካ ምክንያት ጥላቻ ያደረባቸውን አካላት ለማገናኘት ይረዳል (ዳዊት ተሾመ 2013)
- ብሄራዊ እርቅ በሚገባከተያዘናከተጠናቀቀአምባገነኖችንሳይቀርነጻየሚያወጣነው ሁሉምተሳታፊስለሚሆንጦርናየጦርወሬዎችታሪክእየሆኑይሄዳሉ ይህመንገድየሰውህይወትምሆነንብረትናሃብትአያጠፋምበመሆኑምይህየፖለቲካመስመርጭስአልባሊባል ይችላል ስለሆነምበሚያስፈራዝምታውስጥያለውንየሰፊውንየኢትዮጵያንህዝብቀልብሊስብይችላል ለመግባባትናለእርቅየሚደረግእንቅስቃሴበዓለምኅብረተሰብዘንድተቀባይነትስላለውአስፈላጊውን ድጋፍናማበረታቻ ማግኘት አይከብድም በመጨረሻምይህየትግልስልትቀጣይነትያለውሰላምናእድገትእንዲመጣ ፈር ይቀዳል (ተክሉ አባተ
2013/2014)
- ቀጣይነት ላለው ሰላምና ጤናማ ማኅበረሰብ ለመፍጠር መግባባትና እርቅ ማድረግ ወሳኝ ነው (ለአዲሲቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቂ አኢጋን 2014)
የሚታረቀው ማንነው?
ይህን ጉዳይ በተመለከተ በቂ ትንተና አልተሰጠበትም:: ጠቅለል ያሉና ግልጽነት የጎደላቸው ሃሳቦች ግን ተቀምጠዋል:: ከአብዛኞቹ ጽሁፎች ጀርባ ተቀምጠው የሚገኙት ነጥቦች እንደሚያመላክቱት ከሆነ እርቅ የሚደረገው ወይም መደረግ ያለበት በመንግስትና በህዝቡ መካከል ነው:: መንግስት በዳይና ህዝብ ተበዳይ ስለሆኑ የሁለቱ መወያየት መግባባትና መታረቅ ወሳኝ እንደሆነ ያብራራሉ:: እንዲሁም አንዱ ህዝብ ወይም ብሄር ከሌላው ጋር በጥርጣሬና በመፈራራት ስለሚኖር መታረቅ እንዳለበትም የሚጠቁሙ አሉ:: በተጨማሪም መግባባትና እርቅ በግለሰቦች መካከል ያለውን ያልጠራ ስሜትም ለማከም ማገልገል እንዳለበት የጠቆሙ አሉ (አኢጋን 2014):: ከዚህ ባለፈ ግን ጉዳዩን ብትንትን አድርጎ ያስቀመጠ ጽሁፍ የለም:: አንዳንዶች (ለምሳሌ ያዕቆብኃይለማርያም 2014) ማንከማንተጣላና ነው እርቅ የሚያስፈልገውብሎመቀለድዋጋእንደሚያስከፍል ሲያስጠነቅቁ ሌሎች (ለምሳሌ ቴዎድሮስ ኪሮስ 2014; ተክሉ አባተ 2014 )ደግሞ በደፈናው በእርቁ መሳተፍ ያለባቸው ተቃዋሚኃይሎችናድምጹንያጠፋውአብዛኛውኢትዮጵያዊ እንዲሁም የፖለቲካእስረኞች መሆን እንዳለባቸው ይጠቁማሉ:: አኢጋን ደግሞ የመጀመሪያ ደረጃ እርቅ የሚያስፈልገው በዘር በቋንቋ በሃይማኖትና በፖለቲካ በሚለያዩ ቡድኖች መካከል ሲሆን ከዚያ ቀጥሎ ብሄራዊ እርቅ መደረግ እንዳለበት ይጠቁማል:: በአጠቃላይ ሲታይ እርቅ የሚያስፈልገው በህዝብና በመንግስት መካከል ብቻ ሳይሆን ወረድ ብሎም በየደረጃው መከናወን እንዳለበት ጽሁፎች ጠቁመዋል:: ይሁን እንጅ መንግስትና ህዝብ ዋናዎቹ እርቅ የሚያስፈልጋቸው አካላት እንደሆኑ ሁሉም ጽሁፎች ያመላክታሉ::
እርቁን ማንያስተባብረው?
ብሄራዊ እርቁን ማን ማስተባበር እንደሚገባው ግልጽ የሆኑ ሦስት ዋና ዋና አማራጮች ተቀምጠዋል:: አንድ እርቁን መጀመርና ማስተባበር ያለበት መንግስት እንደሆነ ያተቱ አሉ (ለምሳሌ ዘላለም እሸቴ 2014; መሳይ ከበደ 2013/2014 እና ገላውዲዎስ አርአያ 2010):: ፍላጎትና ዝግጁነት ካለው መንግስት ካለበት ብሄራዊ ኃላፊነትና ካለው አቅም አኳያ ይህን የማስተባበር ሥራ ቢወስድ እንደማይከብደው ይገመታል:: ሁለት እርቁን መምራት ያለባቸው ተቃዋሚየፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው የሚሉም አሉ (ለምሳሌ ዋለልኝመኮንን 2012እና ቴዎድሮስኪሮስ 2014):: ይህ አማራጭ ከፖለቲካው ሜዳ በመንግስት እየተገፉ ያሉት ኃይሎች ሂደቱን እንዲመሩት ያመቻቻል:: ሦስት መንግስትና ተቃዋሚየፖለቲካ ፓርቲዎች ዋና የእርቁ አካል ስለሆኑና በዳይና ተበዳይም ስለሆኑ ነጻና ገለልተኛ ኢትዮጵያውያንን ያቀፈ አስታራቂ ግብረ ኃይል የእርቁን ሂደት መምራት አለበት የሚሉም አሉ (ለምሳሌ ተክሉ አባተ 2013 2014)::
ከነዚህ አማራጮች ለየት ያሉም አሉ:: ሁሉን አቀፍ የምክክር ጉባዔ እንዲጠራ ያሳሰቡም አሉ (ሰሎሞን ታረከኝ 2011):: መገናኛ ብዙኅን አስተዋጽዖ ማድረግ እንደሚችሉ ቢጠቀስም ሂደቱን ማን እንደሚመራውና እንደሚጀምረው ግን ግልጽ አይደለም:: እንዲሁም ወጣቱ ትውልድ ወደብሄራዊ እርቅ የሚያደርሰውን ውይይትና ምክክር በበላይነትና በባለቤትነት መምራት እንዳለበት ያሳሰቡ አሉ (አለማዬሁገብረ ማርያም 2012):: የተማረው ወጣቱ ትውልድ የትናንቱ ትውልድ ከሚዳክርበት የግራና የቀኝ የፖለቲካ አመለካከት ነጻ ሆኖ የእርቁን ሂደት ቢመራው እጅግ እንደሚሻል ተጠቁሟል:: ይህ እንዴት መካሄድ እንዳለበትም የመነሻ ሃሳቦች ተሰጥተዋል::
እርቅ እንዴት ይካሄድ?
ብሄራዊ መግባብትና እርቅ እንዴት መካሄድ እንዳለበት በርከት ያሉ ትንተናዎች ተሰጥተዋል:: ብዙዎች (ለምሳሌ ተክሉ አባተ 2014; ዘላለም እሸቴ 2014; ሰሎሞን ታረከኝ 2011; አለማዬሁ ገብረ ማርያም 2012; ገላውዲዎስ አርአያ 2010) ከእርቅ በፊት ቀጣይነት ያላቸውና ሁሉን አቀፍ ክርክሮችና ውይይቶች መካሄድ እንዳለባቸው ጠቁመዋል:: ብሄራዊ ክርክሮችና ውይይቶች መንግስትናተቃዎሚድርጅቶችንበእኩልነትየሚያስተናግዱ: የእያንዳንዳቸውንጠንካራናደካማጎንመለየት የሚያስችሉ: እንዲሁም በእውነት ላይ የተመረኮዙ መሆን እንዳለባቸው ተጠቁሟል:: ሌሎች ስለእርቅ ሂደት የተዘረዘሩ ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው::
- በውይይቶች ጊዜ እውነታን መለየትና እውቅና መስጠት (ያዬ አበበ 2014)
- ሊያጋጥሙየሚችሉችግሮችንቀድሞመለየት:ከዚያምየስምምነትሰነድመፈራረም (ገለታው ዘለቀ 2014)
- ችግሮችንመመርመር:ተጎጅዎችንመለየት (ዳዊት ተሾመ 2013)
- የተሰሩ ወንጀሎችንመለየት:መከላከያናደህንነትተቋማትንገለልተኛማድረግ:በነጻየመናገርመብትማስከበር (ዋለልኝ መኮንን 2012)
- መጀመሪያ ወጣቶች ኢ-መደበኛ ውይይቶችን በአካባቢያቸው መጀመር: ንቃተ ኅሊናን የሚያዳብሩ መርሃ ግብሮችን ማዘጋጀ: ውይይቶች ግልጽነትን ዲሞክራሲያዊ አሠራርን የተከተሉ: ሰብአዊ መብቶችንና ነጻነትን ማዕከል ያደረጉ ይሁኑ:: የራስን ችሎታና አቅም መመዘን: ያሉትን ተቋማት ለዚሁ ዓላማ መጠቀም: ከትናንቱ ትውልድ የአዙሪት ፖለቲካ መጠንቀቅና ከስህተቱ መማር (አለማዬሁ ገብረ ማርያም 2013)
- መንግስት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለአገር እድገት አስተዋጽዖ እንደሚያደርጉ ይመን:: እነሱንም ከማሳደድና ከመፍራት ይልቅ ያቅርባቸው:: በዘር ላይ የተመሰረተውን የፌደራል አወቃቀር እንደገና ያጢነው (ገላውዲወስ አርአያ 2010)
- የታሰሩትን ጋዜጠኞች፣የፖለቲካፓርቲናየሃይማኖትመሪዎችናአባላትንበሙሉመፍታት፤ የጸረ-ሽብርተኛአዋጅመሰረዝ፤እና የፖለቲካፓርቲዎችናየሕዝባዊድርጅቶችአባላትናመሪዎችንበሽብርተኛነትየተፈረጁትንምአጠቃሎየያዘአንድጉባዔበአዲስአበባማካሄድ (ያዕቆብ ኃይለ ማርያም 2014)
- የብሄራዊእርቅመድረኮችይዘጋጁ (ቴዎድሮስ ኪሮስ 2014)
- ከልብ የሆነ ይቅርታመጠየቅናማድረግ (አኢጋን 2014) እርቅና ፍትህ
ብሄራዊ መግባባትና እርቅ በሚጀመርበት ጊዜ የፍትህ አገሯ ወዴት ይሆናል? ይህ ጥያቄ ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ አኳያ በቂ መልስ ያገኘ አይመስልም:: ከ18ቱ መጣጥፎች ውስጥ ሦስት የሚሆኑት ብቻ ይህን ጉዳይ በግልጽ አንስተዋል:: በጣም ለተበደሉ ወገኖች ፍትህ (ለምሳሌ ካሳ) መደረግ እንዳለበት ጠቆም ያደረጉ አሉ (ያዬህ አበበ 2014; አኢጋን 2014):: በጣም የተበደሉት ወገኖች እነማን እንደሆኑና ምን አይነት ካሳ በማን መሰጠት እንዳለበት ግን የተብራራ ነገር የለም:: ከሁሉም ጽሁፎች ገለታው ዘለቀ (2014 ገጽ 4)የጻፉት የእርቅና የፍትህ ግንኙነት እጅግ በተሻለ መልኩ እንደሚከተለው ያብራራል:: ዋናው መልእክት እርቅ በሚደረግበት ጊዜ እንደአስፈላጊነቱ ፍትህም ሥራ ላይ ሊውልበት የሚችል እድል እንዳለ ያመላክታል:: የእርቅና የፍትህ ውሳኔዎች በአንድ ላይ ተጣጥመው መሄድ እንደሚችሉ ባህላችንን በምሳሌነት እያነሳ ይተነትናል::
በስምምነትላይየተመሰረተባህላዊውህደትብሄራዊእርቅንበኢትዮጵያየሚያየውእንደዚህነው።በዚህጽንሰሃሳብመሰረትብሄራዊ እርቁሪስቶሬቲቭጀስቲስንመሰረትያደረገናበሚያድግዴሞክራሲችግሮችንሊፈታየሚችልስምምነትማለትነው።ይህማለትግን ሪትሪቢዩቲቭጀስቲስቦታየለውምማለትኣይደለም።በኣሁኑሰዓትበከፍተኛሙስናናከፍተኛወንጀልእየፈጸሙያሉሰዎችይህንን ኣሳባችንንእያዩእንደጅልነትኣይተውከስልጣንእስኪወርዱበግፋቸውእንዲቀጥሉበርኣይከፍትም። የብሄራዊእርቅሰነዱእንደነዚህኣይነትሰዎችንበቡድንእያየሳይሆንበግለሰብደረጃወደፍርድሊያመጣቸውመቻሉኣያጠያይቅም። እንደቡድንእንደሃገርኢኮኖሚያዊችግሮቻችንንዝግእያለሊሰራጭበሚችልየሪዲስትሪቢዩሽንዘዴተመጣጣኝእድገትለማምጣት መስማማት፣ፖለቲካዊተሳትፎንከባህላዊውህደትስምምነትኣንጻርኣይቶከብሄርፖለቲካኣውጥቶበኣንድብሄራዊማንነትስር ለመገንባትመስማማት፣ዋናየሃገሪቱንቋንቋዎችንቁጥርመጨመርኣጠቃላይፈውስንለማምጣትይጠቅማል። ኢትዮጵያሪስቶሬቲቭጀስቲስላይእንድታተኩርየሚያደርጋትለዘላቂሰላምናልማትኣንድነትየሚረዳትሲሆንይህየፍትህኣሰጣጥዘዴ በኢትዮጵያቡድኖችዘንድየተባረከናየሚበረታታነው።የኦሮሞስርዓትንብናይለሪስቶሬቲቭጀስቲስትልቅቦታኣለው።ይቅርማለትን፣ በዳዩንከመቅጣትይልቅተበዳዩንመካስንያበረታታል።ኣማራውኣካባቢያለውንየሽምግልናስርዓትስናይበኣብዛኛውሪስቶሬቲቭ ጀስቲስ የሚበረታታበት ሁኔታ ኣለ። በደቡብ፣ በምስራቅ በተለይም በሶማሌ ክልል ይህ የፍትህ ስርዓት ከፍተኛ ተጽእኖ ኣለው ገለታው
የማጠቃለያሃሳቦች
ይህጥናትብሄራዊ መግባባትና እርቅን በተመለከተ በርካታ ጠቅለል ያሉ ጉዳዮችን ዳሷል:: ዝርዝር ትንተናዎችን ከዚህ በታች ከተዘረዘሩት መጣጥፎች ማግኘት ይቻላል:: ለማጠቃለል ያህል ግን ጥቂት ነጥቦችን ማንሳት ያስፈልጋል::
አንደኛ ምንም እንኳን የተዳሰሱት 18ቱ መጣጥፎች የብሄራዊ መግባባትና እርቅን ጠቀሜታና አስፈላጊነት ከሌሎች የትግል ስልቶች ጋር በማነጻጸርና በማወዳደር ለማቅረብ መሞከራቸው ክፉ ባይሆንም ጉዳዩን በሌላ መነጽር መመልከቱ ይበልጥ ጠቃሚ ነው:: ብሄራዊ መግባባትና እርቅ ተጀምሮ የተወሰነ አጓጊ ደረጃ እስኪደርስ ድረስ ሌሎችን ትግሎች ማቆም ላያስፈልግ ይችላል:: ሌሎች ትግሎች (ለምሳሌ የተቀናጀና ደረጃ በደረጃ የሚመራ ህዝባዊ እምቢተኝነት http://tekluabate.blogspot.no/2014/08/blog–post_6.html#more) ምናልባትም መንግስት የእርቁን ጉዳይ በሚገባ እንዲያጤነው ሊያስገድዱት ይችላሉ:: በመሆኑም የእርቅን ጠቀሜታ ለማውሳት ሌሎች ትግሎችን ማኮሰስ የግድ አይጠበቅም::
ሁለተኛ የተወሰኑ ጽሁፎች ህዝብ ለህዝብ መታረቅ እንዳለበት አሳስበዋል:: ምንም እንኳን ሃሳቡ በራሱ ክፉ ባይሆንም ለበርካታ ችግሮች ሁሉ ተጠያቂ የሆነውን አካል ማለትም መንግስትን ላላ አርገን እንድንይዝ የሚጋብዝ :: በመጀመሪያ ደረጃ ህዝብ ለህዝብ ሊጣላ አይችልም:: ከበስተጀርባ ያሉ ተንኳሽ የመንግስት ፖሊሲዎችና ፕሮፓጋንዳዎች የህዝብን ልብ ይከፍላሉ:: መንግስት ከትንኮሳው ሁሉ ታቅቦ ህዝቦች በሰላምና በአንድነት እንዲኖሩ ቢሰራ በአጭር ጊዜ ውስጥ የነበረን መከባበርና መተሳሰብ ይመለሳል:: ስለዚህ መታረቅ ያለበት መንግስ ከህዝብ ጋር ነው ብዬ አምናለሁ::
ሦስተኛ መንግስትም ሆነ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች እውነተኛ እርቅን ጀምረው ማስተባበር ይችላሉ ማለት ዘበት ነው:: መንግስት እንደግለሰብ ቂመኛ በቀለኛና ትምክህተኛም ነው:: ለተቃዋሚዎች ያለው ንቀትና ጥርጣሬ መጠን የለውም:: እርቅን እሱ ቢጀምር የመሸነፍና የመዋረድ ያህል ይመለከተዋል:: ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ቢሆኑ ከመንግስት ጋር ያላቸው ቅራኔ እርቅ ለመጠየቅ የሚያበቃ አይመስልም:: ሰጥቶ የመቀበልና የማሳመን ችሎታና ፍላጎት እስካሁን አላየንም:: በመሆኑም ሌላ ገለልተኛና አንጻራዊ በሆነ መልኩ ንጹህ ኢትዮጵያውያን የተሰባሰቡበት አካል ያስፈልጋል:: ይህን አካል የሚያቋቁመው አካል: የሚቋቋምበት መስፈርት: የሚኖረው ዝርዝር የሥራ ድርሻ: የሚጠቀማቸው ዘዴዎች: ወዘተ ግን ጥርት ብለው ለውይይት ቢቀርቡ የተመረጠ ነው እላለሁ:: እንዲሁም ፍትህና እርቅ ምን ያህል የሚዛመዱና የሚቃረኑ እንደሆነ የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታዎች ግምት ውስጥ በማስገባት አስቀድሞ መተንተን ያስፈልጋል::
በአጠቃላይ ይህ አስተባባሪ ኃይል ከእርቅ በፊት በእርቅ ጊዜና ከእርቅ በኋላ ሊሟሉ የሚገባቸውን ሁኔታዎች እጅግ በዝርዝር አዘጋጅቶ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አቅርቦና በውይይት አዳብሮ ሊንቀሳቀስ ይገባል:: ይህ ቀላል ሥራ ስላልሆነ የሚመረጡት ሰዎች ስሜታቸውን የሚቆጣጠሩና የሞራል ብስለት ያላቸው: አዋቂዎችና አስተዋዮች: እንዲሁም የመግባባትና ጫናን የመቋቋም አቅም ያላቸው ሊሆን ይገባል:: ልዩ ልዩ አይነት መስዋዕትም ለመክፈል የተዘጋጁ መሆን አለባቸው:: በመሆኑም ብሄራዊ መግባባትና እርቅ በብርቱ ልፋትና መከራ የሚመጣ እንጅ እንደሚታሰበው ‘ሰላማዊ’ ብቻ ላይሆን ይችላል::
የመጀመሪያው ችግር የሚሆነው ይህን አስታራቂ ኃይል ማቋቋም ነው:: ማን ነው ይህን ሊያነሳሳው የሚችለው? በተለያዩ አካላትስ ተቀባይነት ይኖረዋል? ፍላጎትና ለኢትዮጵያ መልካም ራእይ ያለው ማንኛውም አካል ሊጀምረው ይችላል:: ቢያንስ ቢያንስ ይህ ጥናታዊ ጽሁፍ የገመገማቸውን 18ቱን በብሄራዊ መግባባትና እርቅ ላይ ያተኮሩ መጣጥፎችን ያቀረቡት ምሁራን በመመካከር ለጉዳዩ የሚሆን መሪ ሃሳብ roadmap ማዘጋጀትና ለውይይት ማቅረብ ይችላሉ:: ጥናቱን በማካሂድበትጊዜየታዘብኩትናወደፊትትኩረትሊሰጠውየሚገባውጉዳይግን አለ::ሁሉምመጣጥፎችራሳቸውንየቻሉናሌላውንለድጋፍምይሁንለትችትበፍጹምየማይጠቅሱናቸው::ስለአንድጉዳይበሚጽፉሰዎችመካከልምንምአይነት ‘መናበብ’እንደሌለአመላካችነው:: ሁሉምየግልሩጫውንተያይዞታል::ይህን አቁመን በአንድ ጉዳይ ላይ የምንጽፍ ሰዎች መናበብ ብንጀምርና የመነሻ ሃሳብ ብናቀርብ ብሄራዊ ግዴታችንን እንደመወጣት ይቆጠራል:: የያዘውን የወረወረ ፈሪ አይባልም!!! ሰላም አንድነትና ብልጽግና ለኢትዮጵያ!
///////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////////
ገንቢ አስተያየት ወይም ጥያቄ ካለዎት በteklu.abate@gmail.com ይላኩ!
ስለብሄራዊእርቅየተጻፉጽሁፎች
በአማርኛየተጻፉ
- ተክሉአባተ 2014 ጎጂባህሎቻችን (የመጨረሻውክፍል).
http://www.ethiomedia.com/14store/gojjee_bahlochachin_final_part.pdf
- ተጋ 2013 አገራችንንበእርቅእንታደጋት”http://www.goolgule.com/reconciliation–the–way–out/ §ያዕቆብኃይለማርያም 2014 ብሔራዊመግባባት ወይስ አገራዊ ውድመት? http://www.zehabesha.com/amharic/archives/33174
- ያዬአበበ 2014 እውነታ + እውቅና + ፍትህ = እርቅ.http://www.65percent.org/files/EwnetaEwqinaFeteh_Yaye_Abebe.pdf
- ዳዊትተሾመ2013 የብሔራዊዕርቅጥያቄናፈተናዎቹበኢትዮጵያ . ክፍል2 http://www.zehabesha.com/amharic/archives/10340
- ዳዊትተሾመ2013 የብሔራዊዕርቅጥያቄናፈተናዎቹበኢትዮጵያ.http://www.goolgule.com/on–thequestion–of–national–reconciliation/
- ገለታውዘለቀ 2014 ኢትዮጵያየብሄራዊእርቅኮሚሽንማቋቋምየሚያስፈልጋትጊዜላይናት.http://www.ethiomedia.com/14store/bherawi_erq.pdf
- Alemayehu G Mariam 2013 Cheetahs, Hippos and Saving Ethiopia.
በእንግሊዝኛየተጻፉ
http://ethiomedia.com/2012_report/4559.html
- Ghelawdewos Araia2010NationalReconciliationandNationalDevelopmentinEthiopia.http://ethiopianunitydiasporaforum.com/news/national–reconciliation–andnational–development–in–ethiopia/
- Mesay Kebede2014 Democracy and its Trade-off: Ethiopia’s Path to National Reconciliation. http://www.zehabesha.com/democracy–and–its–trade–off–ethiopias–path–to–national–reconciliation/
- Messay Kebede 2013 Which Way Ethiopia: Revolution, Civil War, or National Reconciliation? http://www.abugidainfo.com/index.php/21346/
- SMNE 2014 Reconciliationhttp://www.solidaritymovement.org/reconciliation.php
- Solomon Tarekegn 2011 A Call for a National Conference to Save Ethiopia!
http://ecadforum.com/2011/01/20/a–call–for–a–national–conference–to–save–ethiopia/
- Teklu Abate 2013 Inclusive discourse: A prelude to national reconciliation.
http://www.zehabesha.com/inclusive–discourse–a–prelude–to–national–reconciliation/§Teodros Kiros 2014 Reconciliation is the language of communicative rationality. http://www.africanidea.org/reconcilation_kiros.html
- Walelgn Mekonnen 2012 It is a time for national reconciliation and accountability.http://www.ethiopianreview.com/mobile/?p=2781
- Zelalem Eshete2014 Ethiopia: Call for Opposition & Government.
http://www.zehabesha.com/ethiopia–call–for–opposition–government/
- Zelalem Eshete2014 Ethiopia: Reconciliation Pyramid.
http://www.zehabesha.com/ethiopia–reconciliation–pyramid–zelalem–eshete–ph–d/