
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ(አብን) የብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፀመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ።
* የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ ጥቅምት 14 ቀን 2013 ዓ.ም እያካሄደ ባለው አስቸኳይ ስብሰባ የአማራን ሕዝብ እየገጠሙት ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ እየተወያየ ይገኛል።
–
በውይይቱ በዋናነት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በአማራዎች ላይ እየደረሰ የሚገኘውን የዘር ማጥፋት ወንጀል እና ሌሎች መዋቅራዊና ሕግ ሰራሽ መገለሎችን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በ «አማራ ክልል» በሚገኙ ከተሞች በመጭው ረቡዕ ጥቅምት 18 ቀን 2013 ዓ.ም እንዲሁም በአዲስ አበባ እሁድ ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም እንዲደረግ ወስኗል።
