November 14, 2020

ራያ ዋጃና ጥሙጋ ቆቦ ወ አዘቦ ጨርጨር መሆኒ እና ባላ ከእልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ በሁዋላ የባርነት ቀንበራቸው ተሰብሯል:: የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አላማጣንና ኮረምን ከህወሀት ሰራዊት ነፃ አድርጎ ግስጋሴውን ቀጥሏል:: በሐገር መከላከያ ሰራዊት፣በአማራ ልዩ ሀይልና በሚሊሻ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል። 

(አብመድ) የሐገር መከላከያ ሰራዊትና የአማራ ልዩ ሀይል የተለያዩ አካባቢዎችን በድል አልፈው ነው ከዘራፊው የትህነግ ልዩ ኃይል ነጻ ያደረጉት።

– የሐገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ልዩ ኃይል በራያ ግንባር ከባድ ጥቃት ሰንዝረዋል። የትህነግ ስግብግቡ ጁንታ ልዩ ኃይል እየተደመሰሰ ነው፤ጉዳትም ደርሶበታል፤ አካባቢውንም ለቆ እየፈረጠጠ ነው።

የአካባቢው ነዋሪዎች እንዳሉት ትህነግ እያራመደ ባለው አምባገነናዊ ስርዓት ግፍ ደርሶባቸዋል።

አሁን ላይ በመከላከያ ሰራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይልና በሚሊሻ አባላት ከትህነግ ከሐዲ ቡድን ነጻ በመውጣታቸው ደስታቸውን እየገለጹ ነው።

የትግራይ ህዝብ የዘራፊውን ትህነግ ቡድን ሐገርን የማፍረስ ተግባር በመቃወም ከመንግስት ጎን መቆም እንዳለባቸውም አሳስበዋል።