«በህወሓት ውስጥ የሚገኘው ጁንታ መወገድ ለትግራይ ሕዝብ እፎይታ ነው» – አቶ አብዱረህማን አህመዲን የቀድሞ የፓርላማ አባልና የኢዴፓ አመራር(ኢ ፕ ድ) ላለፉት አርባ ዓመታት በትግራይ ምድር ተፈጥሮ የትግራይን እናቶች ልጅ አልባ ያደረገውንና በአሁኑ ወቅትም በዕድሜ ጨቅላ የሆኑ ሕፃናትን መሳሪያ አስታጥቆ የሚንቀሳቀሰው የህወሓት ጁንታ ቡድን መወገድ ለትግራይ ሕዝብ እፎይታ መሆኑን የቀድሞ የፓርላማ አባልና የኢዴፓ አመራር የነበሩት አቶ አብዱረህማን አህመዲን አስታወቁ ።–

አቶ አብዱረህማን ቡድኑ በሰሜን እዝ ላይ የፈፀመውን ጥቃት አስመልክቶ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ በህወሓት ውስጥ የሚገኘው ጁንታው ቡድን ከአፈጣጠሩ ጀምሮ ሰብዓዊነት የጎደለውና ከሕዝባዊ ዓላማ ይልቅ የቡድን ፍላጎትን ለማሳካት ሲታትር የኖረ እና የትግራይን ሕዝብ ለበርካታ ችግሮች የዳረገ ነው።–ቡድኑ ከጥንስሱ ጀምሮ የገዛ ጓዶቹን ጭምር ደም በማፍሰስ የመጣና ባለፉት 27 ዓመታትም በርካታ ኢትዮጵያውያንን ለመከራና ለስቃይ የዳረገ ግፈኛ ቡድን መሆኑን የተናገሩት አቶ አብዱረህማን፣ አሁን ደግሞ የጥቂት ግለሰቦችን ወንጀል ለመደበቅ ሲባል ሕፃናትን መሳሪያ አስታጥቆ በማሰለፍ ደም ለማፋሰስ ቆርጦ የተነሳ አረመኔ ቡድን ነው ብለዋል።–ቡድኑ አብዛኛውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያገለለ እና ጥቂቶችን ብቻ ተጠቃሚ ያደረገ የኢኮኖሚ ሥርዓት በመዘርጋት ዜጎች በሀገራቸው እኩል ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ሲታትር ከመቆየቱም ባሻገር ሀገር አስተዳድራለሁ በሚል ሽፋን የሰዎችን ጥፍር ሲነቅል፤ ሲያኮላሽ፤ ከአራዊት ጋር ሰዎችን ሲያስርና ሲገድል የነበረ ጨካኝ ሥርዓት መሆኑንም አመልክተዋል።–እኛ ከሌለን ኢትዮጵያ መኖር የለባትም በሚል አስተሳሰብ ኢትዮጵያን ለማፈራረስና ሕዝቦች ሀገር እንዳይኖራቸው ለማድረግ አበክሮ ሲሰራ የነበረ ቡድን መሆኑን የተናገሩት አቶ አብዱረህማን ፣እኛ ከሌለን ኢትዮጵያ ትፈርሳለች የሚል ድሃ አስተሳሰብ በመያዝ ለዘመናት ሲንቀሳቀሱ ቢቆዩም እነሱ በሌሉበት የተሻለች ኢትዮጵያን መገንባት እንደሚቻል ፍንጮች እየታዩ መሆኑን ጠቁመዋል።–https://www.press.et/Ama/?p=41778