
Ethiopia: WHO director-general works as TPLF diplomat
የሀገር መከላከያ ሰራዊት በህወሀት ቡድን ላይ ህግ የማስከበር ዘመቻ ከጀመረበት ዕለት አንስቶ ዶ/ር ቴውድሮስ ሲያደርጉት የነበረውን እንቅስቃሴ የኢትዮጵያ መንግስት ጠንቅቆ ያውቃል – አንድ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ኢትዮ ኤፍ ኤም – የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም ለህወሀት ቡድን የዲፕሎማሲ ስራ ሲሰሩ እንደነበር ተገለፀ፡፡
–

ዶክተር ቴድሮስ አድሀኖም ለህወሀት ቡድን ዲፕሎማሲያዊ እና ወታደራዊ ድጋፍ እንዲደረግ የአለም መንግስታትን በመጠየቅ እረገድ ሙሉ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑን አንድ ከፍተኛ ባለሥልጣን ገልፀዋል፡፡
–
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣን ለአናዶሉ ኤጀንሲ እንደተናገሩት የሀገር መከላከያ ሰራዊት በህወሀት ቡድን ላይ ህግ የማስከበር ዘመቻ ከጀመረበት ዕለት አንስቶ ዶ/ር ቴውድሮስ ሲያደርጉት የነበረውን እንቅስቃሴ የኢትዮጵያ መንግስት ጠንቅቆ ያውቃል ብለዋል፡፡
–
የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በህወሃት ላይ የሚወስደውን ወታደራዊ እርምጃ እንዲያስቆሙ እንዲሁም በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲያሳድሩ ሲጠይቁ ነበር ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል፡፡
–
እንደ አውሮፓውያኑ ከ 2017 ጀምሮ በአለም ጤና ድርጅት (WHO) ውስጥ እያገለገሉ የሚገኙት ዶ/ር ቴድሮስ የህወሀት ቡድን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል ሆነው ሲያገለግሉ እንደነበር ይታወቃል፡፡
–
እንደ አውሮፓውያኑ ከ 2005 እስከ 2012 የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር እንዲሁም ከ 2012 እስከ 2016 ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ነበሩ፡፡
–
ኢትዮ ኤፍ ኤም and Source – https://www.aa.com.tr/en/africa/ethiopia-who-director-general-works-as-tplf-diplomat/2046193