ታህሳስ 04/2013 ዓ.ም

ባህር ዳር በወልቃይት ጠገዴ የአዲረመፅ/ወፍ አርግፍ ከተማ ነዋሪዎች ከትሕነግ የግፍ አገዛዝ ነፃ በመሆናቸው ደስታቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ።

ወጣቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ሴቶች እና የሃይማኖት አባቶች እየተሳተፉበት በሚገኘው በዚህ ሰልፍ፣ “ወታደራዊው ድል በፖለቲካውም ይደገማል”፣ “ፀባችን ከትግራይ ሕዝብ ጋር ሳይሆን ከጨፍጫፊው እና ከከሀዲው ትሕነግ ጋር ነው”፣ “የወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት ሕዝብ ወደ ቀደምት ማንነታችን በመመለሳችን ደስተኞች ነን”፣ “የማይካድራ ጭፍጨፋ ተሳታፊዎች ለፍርድ ይቅረቡ” እና “ከሀዲው ጁንታ በአሸባሪነት ይፈረጅ” የሚሉ መፈክሮች አሰምተዋል።

ዘጋቢ፡- ማርሸት ጽሀው