February 5, 202

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስልክ ደውለው አነጋግረዋቸዋል።

የዩናይትድ ስቴትስንና የኢትዮጵያን ግንኙነቶች አስፈላጊነት ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በአፅንዖት ያነሱላቸው መሆኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ቢሮ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ባወጣው ፅሁፍ አስታውቋል።

Image

Secretary Antony Blinken@SecBlinken

US government account

I spoke with Ethiopian Prime Minister @AbiyAhmedAli to express concern about the crisis in Tigray and urge safe and unhindered humanitarian access to prevent further loss of life. Despite current challenges, the U.S. stands ready to support reforms and peaceful elections.

1:29 PM · Feb 4, 2021

5.5K4KCopy link to Tweet

ትግራይ ውስጥ ያለው ሰብዓዊ ቀውስ በእጅጉ የሚያሳስባቸው መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ መግለፃቸውንና ሌላ የህይወት መጥፋትን ለማስቀረት እንዲቻል መንግሥቱ ፈጥኖ መሉና ያልተገደበ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ እንዲያደርግ ማሳሰባቸውን ቃል አቀባዩ አመልክቷል።

ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ የለውጥ አጀንዳ፣ ለመጭው ብሄራዊ ምርጫ፣ ለአካባቢያዊ ሰላም፣ ፀጥታና ደኅንነት፣ ለዴሞክራሲና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለፍትኅና ለተጠያቂነት መስፈን፣ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ኢኮኖሚያዊ ብልፅግና ድጋፏን መስጠቷን እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቶኒ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በድጋሚ ያረጋገጡላቸው መሆኑንም የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ፅሁፍ አስታውቋል።

Image

Abiy Ahmed Ali

🇪🇹

@AbiyAhmedAli

Thank you @SecBlinken for commitment to support #Ethiopia’s deep reforms that we will pursue undetterred. Our aspirations to democratize and build a multidimensional prosperous & peaceful country for all will be enhanced through strengthened Ethiopia-US relations.

12:04 AM · Feb 5, 2021

3.6K 1.1K Copy link to Tweet