የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንተኒ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስልክ ደውለው አነጋግረዋቸዋል።
የዩናይትድ ስቴትስንና የኢትዮጵያን ግንኙነቶች አስፈላጊነት ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በአፅንዖት ያነሱላቸው መሆኑን የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ቢሮ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ባወጣው ፅሁፍ አስታውቋል።

Secretary Antony Blinken@SecBlinken
I spoke with Ethiopian Prime Minister @AbiyAhmedAli to express concern about the crisis in Tigray and urge safe and unhindered humanitarian access to prevent further loss of life. Despite current challenges, the U.S. stands ready to support reforms and peaceful elections.
ትግራይ ውስጥ ያለው ሰብዓዊ ቀውስ በእጅጉ የሚያሳስባቸው መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ መግለፃቸውንና ሌላ የህይወት መጥፋትን ለማስቀረት እንዲቻል መንግሥቱ ፈጥኖ መሉና ያልተገደበ ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲደርስ እንዲያደርግ ማሳሰባቸውን ቃል አቀባዩ አመልክቷል።
ዩናይትድ ስቴትስ ለኢትዮጵያ የለውጥ አጀንዳ፣ ለመጭው ብሄራዊ ምርጫ፣ ለአካባቢያዊ ሰላም፣ ፀጥታና ደኅንነት፣ ለዴሞክራሲና ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለፍትኅና ለተጠያቂነት መስፈን፣ ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ኢኮኖሚያዊ ብልፅግና ድጋፏን መስጠቷን እንደምትቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቶኒ ብሊንከን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በድጋሚ ያረጋገጡላቸው መሆኑንም የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ፅሁፍ አስታውቋል።


Thank you @SecBlinken for commitment to support #Ethiopia’s deep reforms that we will pursue undetterred. Our aspirations to democratize and build a multidimensional prosperous & peaceful country for all will be enhanced through strengthened Ethiopia-US relations.