
ህወሓትን ከመሰረቱ ጥቂት ሰዎች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ግደይ ዘርዓጽዮን ይናገራሉ፡-
ህወሓቶች የዘመናት ድርጊታቸው ለዚህ አሁን ላሉበት ውርደት፣ ሞትና መደበቅ ዳርጓቸዋል፤ በተንኮልና በሴራ ራሱን አጥፍቷል፤
ትግሉ የተጀመረው ደርግ ወደ ስልጣን ከመምጣቱ በፊት ተራማጅ በሆኑ የትግራይ ተወላጅ ወጣቶች አማካይነት ማህበረ ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ (ማገብት) የሚል ማህበርን በመመስረት ነው፤
በህወሓት ውስጥ ማርክሲስት ሌሊኒስት ርዕዮተ ዓለም ሲመሰረት በወቅቱ በተለይም ጥቂቶች የስልጣን መወጣጫ ነበር ያደረጉት፤
ስልጣናቸውን ለማሰንበት ሲሉ መወንጀል ጀመሩ፣ እንኳን በድርጅቱ ውስጥ ሃሳብን አንስቶ የመከራከር መብቱ ይቅርና የሚነሱ ሀሳቦችን በማዋደቅ ልዩነቶች እንዲሰፉ ይደረግ ነበር፣
የአልባንያ ተከታዮች ነን፤ እኛ ማርክሲስት ሌሊኒስት ነን፤ ብለን አላማችንን ለዓለም ህዝብ ማሳወቅ አለብን የሚል አመለካከት ነበራቸው፤
ድርጅቱ ውስጥ የምንሰራው በእምነት ነው፤ ጓደኞቻችን በእኛ ላይ እንደዚህ ዓይነት ሴራ ይሸርባሉ ብለንም በፍጹም አናስብም ነበር፤
ሴራቸውማ በጣም ከባድ ነው፤ እርስ በእርሳቸውም እየተባሉ ነው እዚህ የደረሱት፤ ኢ- ዲሞክራቲክ፤ አፋኝ ሌላ ተቃዋሚ እንዳይታይ የሚያደርግ፤ ለይስሙላ ምርጫ የሚያደርግ፤
በጎን ደግሞ ግልጽና ፍትሃዊ እንዳይሆን ጠንካራ ስራን የሚሰራ፤ ሀገሪቱ በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር ስር እንድትወድቅ ያደረገ የተቃወሙትን የገደለ፤ ያፈነ፤ ያሰረ፤ ያሰደደ ነበር፣
ለውጡን አብዛኛው የአገሪቱ ህዝብና ተቃዋሚ ፓርቲዎች በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት ተቀብለዋል፣
ዝርዝር ዘገባውን ሊንኩን ተጭነው ያገኙታል
https://www.press.et/Ama/?p=41395
