15/02/2021

This image has an empty alt attribute; its file name is FB_IMG_1613383047339-300x248.jpg

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከተባለው  እስከ አረና፤  ከትዴት እስከ ትግራይ ብልጽግና፤ ከውናት እስከ ሳልሳይ ወያነ፤ ከባይቶና እስከ  ፈንቅል ያሉት የትግሬ ብሔርተኞች ሁሉ የስልጣን ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር በአማራ ጥላቻቸው የፈጠራቸውን ሕወሓትን የሚያስንቁ ስለመሆናቸው ጥርጥር የለውም። ሁሉም ሕወሓት የዘረፈው ሁሉ ይገባናል የሚሉ ቀማኞች ናቸው።

ሁሉም የመንፈስ አባታቸው ሕወሓት በቅኝ ግዛት ከያዘው ከማይካድራ 1100 አማራዎችን ብቻ ጨፍጭፎ በመፈርጠጡ ጥንቢራቸው እስኪዞር ድረስ የሚበሳጩ ናቸው። እነሆ ያንን የበቀል ቁጭታቸውን ለመወጣት ከቅኝ ግዛታቸው ነጻ ወደወጡት የደም ምድሮች ለመመለስ ጥርሳቸውን በመንከስና ዐይናቸውን በማጉረጥረጥ ላይ ናቸው!

እነዚህ የሕወሓት ቅጥያዎች የአሁኑ የአማራ ትውልድ እንደ ብአዴኑ ትውልድ የአማራ ጠላቶች በአማራው መቃብር ላይ ፍላጎታቸውን እስከጥግ ድረስ ሲያስፈጽሙ ዝም ብሎ የሚያይ፤ የጠላት ጉዳይ ለማስፈጸም እስኪያልበው ድረስ የሚታዛዝና  በልቶ ማደርን ብቻ የሕይዎት መመሪያው ያደረገ አለመሆኑን የተገነዘቡት አይመስልም።

የአሁኑ  የአማራ ትውልድ ካሁን በኋላ ከሕወሓት ቅኝ ግዛት ነጻ ያወጣቸውን ወረዳዎቹን ክንዱን ሳይንተራስ ወደ ቅኝ ግዛት እንዲመለሱ የሚፈቅድ ምስለ ብአዴን አለመሆኑን ደቂቀ ሕወሓት ሁሉ ቢያውቁት ይመከራል።

የሆነው ሆኖ አብርሀ ደስታን ጨምሮ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ሁመራ የትግራይ እንደነበሩ የስናፍጭ ቅንጣት ያህል የታሪክ እውነት አለኝ የሚል የትግሬ ብሔርተኛ ወይም የታሪክ ምሑር ቢኖር ቢፈልግ በግሉ፤ ቢያሻው በጋራ በመሆን በመረጠው ሜዲያ  ወይም የቴሌቭዥን ጣቢያ እንቅረብና እስቲ  በግልጽ እንከራከር፤ ግብዣዬም ነው።