Skip to content
የኢሕአፓ የኢንዱስትሪ ክፍለ ኢኮኖሚ ፖሊሲ መሰረታዊ ነጥቦች !
1.የኢንዱስትሪው ክፍለ ኢኮኖሚ በነፃ ገበያ ኢኮኖሚ መርህ እንዲንቀሳቀስ ማድረግ !
2.የግል ባለሀብቶች ስላልተሰማሩባቸዉና ለሀገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም እጅግ በጣም አስፈላጊ ስለሆኑ በመንግሥት ቁጥጥር ና አስተዳደር ስር እንዲዉሉ ከተደረጉት በስተቀር በኢንዱስትሪው ክፍለ ኢኮኖሚ የግል ባለንብረትነት መብት እንዲከበር ማድረግ !
3.የሀገር ዉስጥ ባለሀብቶች የኢንዱስትሪ መስክ ተሳትፎ እንዲያድግ የተጠና ድጋፍ ማድረግ ፤ሚዛናዊ (የተመጣጠነ ) የግብር ስርዓት በማዉጣት የሀገር ዉስጥ የኢንዱስትሪ ባለሀብቶችን መደገፍ !
4.በሀገሪቱ ዉስጥ የሚገኙ በመካከለኛ ና በከፍተኛ ደረጃ የተማሩ የሰው ሀይል ሀብቶችን አቅም በሰፊው የሚፈልጉ ና የሀገር ዉስጥ ጥሬ እቃዎችን በግብአትነት የሚጠቀሙ ለወጣቶች ና ለወጣት ሴቶች ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥሩ ኢንዱስትሪዎችን ማስፋፋት ና ማዘመን!
5.ኢንዱስትሪዎች ና ፋብሪካዎች በተወሰኑ ቦታዎች ብቻ ሳይከማቹ ጥሬ እቃዎች ና ሊያሰሩ የሚችሉ ሁኔታዎች ባሉባቸው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲቋቋሙ ማድረግ !
7.በርካታ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ግንባታ በግል ባለሀብቶች ና በመንግሥት ማካሄድ !
8.የዉጪ ሀገር ባለሀብቶች ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጥቅም ጋር በማይጋጭ መልኩ በተለያዩ የኢንዱስትሪ መስኮች ና የስራ ዘርፎች እንዲሰማሩ ማበረታታት !
#ኢሕአፓ ለተሻለች ኢትዮጵያ !
ለነገዋ ብሩህ ኢትዮጵያችን – ኢሕአፓ ይሁን ምርጫችን
Like this:
Like Loading...