March 17, 2021

ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ትናንት ለሕክምና ወደ ውጭ ሀገር ሊሄዱ ሲሉ የመንግሥት ደኅንነቶች እንዳገዷቸው ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በጻፉት ደብዳቤ መግለጻቸውን ፓርቲያቸው በፌስቡክ ገጹ ካሰራጨው ደብዳቤ ተመልክተናል፡፡ ለረጅም ጊዜ በውጭ ሀገር ሕክምና እንዳያገኙ በመከልከላቸው ሕይወታቸው አደጋ ላይ እንደሆነ ልደቱ ገልጸዋል፡፡ በተከሰስኩባቸው ወንጀሎች ነጻ መሆኔን ፍርድ ቤት ስለወሰነልኝ እና እገዳው የተጣለብኝ በፖለቲካ አመለካከቴ በመሆኑ፣ ኮሚሽኑ አስፈላጊውን እገዛ ያድርግልኝ ሲሉ ተማጽነዋል፡፡

No photo description available.