ሱዳንን በሚመለከት በዲፕሎማስው ሰፊ ስራ እየሰራን ነው፡፡ ከሱዳን ጋር ጦርነት መጀመር አያስፈልግም ኪሳራ ነው ፤
ሱዳንም አሁን ባለው ሁኔታ ከጎረቤት አገር ጋር ለመዋጋት በሚያስችል ቁመና ላይ አይደለም ያለችው ፡፡ብዙ የውስጥ ችግር አለባት፤
ኢትዮጵያም አሁን ባለው ሁኔታ ከሱዳን ጋር ለመዋጋት ብዙ ችግር አለባት፤ ስለዚህ ጦርነቱ ለሁለታችንም አያስፈልገንም፤
ችግሩን በንግግር፣ በውይይት፣ በድርድር መፍታት ነው የሚያስፈልገው፤ ያ ተጀምሯል፤
ከአጼ ሚኒሊክ ዘመን ጊዜ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ በንግግር ያለጉዳይ ነው፤ በእኛ በኩል በምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ የሚመራ ኮሚቴ በእነሱ በኩልም በሚንስትር የሚመራ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራበት ነው፤
ላለፈው አንድ አመት ያህል ስራ ስንሰራ ቆይተናል፤ አሁን ይሄ የሕግ ማስከበሩ ስራ ሲጀመር ነው የተቋረጠው፡፡ በዚህ ወቅት እነሱ ወደማይገባ መንገድ ሄዱ፤
እኛ ለዚህ የሰጠነው ምላሽ በሁለቱ ሕዝቦች መካከል ውጊያ አያስፈልግም፤ በውይይትና በድርድር እንፍታው ነው ያልነው፤
ይሄን ስንልም የእኛ አርሶ አደሮች ተፈናቅለዋል፤ ማሳቸው ተቃጥሏል፤ ቤታቸው ተቃጥሏል፤ በደል ደርሶብናል፤ ያም ሆኖ አንዋጋ እያልን ነው፤ ውጊያ ስለማይጠቅመን፤
ይሄ እንደተጠበቀ ሆኖ ሱዳን ከሌሎች ጋ ወዳጅነት ፈጠረች የተባለው ሱዳን ከማንኛውም አገር ጋ ወዳጅ መሆን ትችላለች፤ የኢትዮጵያ ጠላት መሆን ግን አትችልም፤
ሱዳን የሚለው ቃል በአርብኛ እና ኢትዮጵያ የሚለው ቃል በግሪክኛ አንድ ነው ትርጉሙ፤ አንድ ሕዝብ ነው፤ የትም አገር ሄዳችሁ ሱዳናዊ ብታዩ በአማርኛ ነው የምታወሩት፤
ኢትዮጵያን ከሱዳን መለየት አይቻልም፤ ከማንኛውም አገር ጋ ወዳጅ መሆን ይቻላል፤ ችግር የለውም፡፤ እኛም ከሌሎች አገራት ጋር ወዳጅ መሆን እንችላለን፤ የሱዳን ጠላት መሆን ግን አንችልም፤
በብዙ ነገር አንድ ሕዝቦች ነን፤ ተከባብረንና ተዋድደን የኖርን ወደፊትም አብረን የምንኖር ሕዝቦች ነን፤
ጉልጉል