May 25, 2021


በአማራ ክልል “ሰሜን ሸዋ ዞን” በቅርቡ በተከሰተው የፀጥታ መደፍረስ አካባቢውን መልሶ ለማቋቋም በክልል ደረጃ የተዋቀረው የቴክኒክ ኮሚቴ የምልከታ ሪፖርቱን ለአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች አቅርቦ ነበር።

በሪፖርቱ መሰረት ፦

– በሰሜን ሸዋ 3 ወረዳዎች ብቻ 281 ሰዎች ተገድለዋል።

– 197 ዜጎች ላይ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል።

– 246 ሺህ 818 ሰዎች እርዳታ ፈላጊ ሆነዋል ፤ 9,661 ዜጎች ከመኖሪያ አካባቢያቸው ተፈናቅለዋል።

– በሸዋ ሮቢት፣ ቀወትና ኤፍራታ ግድም 4 ትምህርት ቤቶች ወድመዋል፤ 7 ትምህርት ቤቶች ደግሞ ንብረታቸው ወድሟል።

– ሶስት የጤና ተቋማት ወድመዋል፤ አንድ ጤና ተቋም ተዘርፏል።

– 7 የእምነት ተቋማት ተቃጥለዋል።

– የውሃ መሰረተ ልማቶች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል።

– አስራ አንድ ሆቴሎች እና አርባ ዘጠኝ የግል መጋዘኖች ተቃጥለዋል።

– እንስሳት መዘረፋቸውና የግብርና መሰረተ ልማቶች ላይ የከፋ ጉዳት ደርሷል።

– የተጎዱ ዜጎችን ለማቋቋምና አካባቢውን መልሶ ለመገንባት ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ያስፈልጋል።

በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የደረሰውን ጉዳት የቴክኒክ ኮሚቴው እያጠናው የሚገኝ ሲሆን ባጭር ጊዜ ሪፖርቱን ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።