19 ጥር 2022, 10:10 EAT
በየዓመቱ ጥር 10 እና 11 በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች ዘንድ በድምቀት የሚከበሩት የከተራና የጥምቀት በዓላት በርካታ ሕዝብ ይታደምባቸዋል። እነዚህ ደማቅ የአደባባይ በዓላት ላይ ከህጻናት አስከ አዋቂዎች ባህላዊ አልባሳትን በመልበስ በየአጥቢያቸው ሚገኙ ታቦታን አጅበው በዝማሬ ወደ ማረፊያቸው በመውሰድ ይመልሳሉ። ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የዓሉን አከባበር የሚያሳዩ ምስሎችን እነሆ።
የምስሉ መግለጫ,አዲስ አበባ የሚገኘው የቦሌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ዘማሪያን በከተራ ዕለት
የምስሉ መግለጫ,የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ
የምስሉ መግለጫ,ጃን ሜዳ አዲስ አበባ
የምስሉ መግለጫ,ከተራ በጎንደር፤ በጥምቀት ዋዜማ በከተራ ዕለተ የጎንደሩ ነዋሪ ከአጼ ቴዎድሮስ ሐውልት ስር ቆሞ
የምስሉ መግለጫ,የአዲስ አበባ ከንቲባ በዓሉን ለማክበር በጎንደር ከተማ ተገኝተዋል። ከንቲባ አዳነች “ጥምቀትን በጎንደር” ለማክበር እንገናኛለን ባልነው መሠረት በጎንደር ተገኝተናል ሲሉ ይህን ጨምሮ ሌሎች ምስሎችን በፌስቡክ ገጻቸው አጋርተዋል።
የምስሉ መግለጫ,የከተራ በዓል በባሕር ዳር ከተማ
የምስሉ መግለጫ,በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ከሚሴ ከተማ
የምስሉ መግለጫ,የከተራ በዓል አከባበር በጎንደር
የምስሉ መግለጫ,የከተራ በዓል አከባበር በምዕራብ ጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ ከተማ
የምስሉ መግለጫ,የከተራ በዓል አከባበር በኦሮሚያ ኢሉባቦራ መቱ ከተማ
የምስሉ መግለጫ,የከተራ በዓል አከባበር ወልዲያ ከተማ
የምስሉ መግለጫ,የጥምቀት በዓል አከባበር በከሚሴ ከተማ
Like this:
Like Loading...