
በትግራይ ተፋላሚ ኃይሎች ተደጋጋሚ ቅሬታ የሚቀርብባቸው የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፤ በአፍሪካ ህብረት በኩል የተሰጣቸው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ኃላፊነት ተራዘመላቸው። የኦባሳንጆ የልዩ ልዑክ ሹመት መራዘሙን የገለጹት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት ናቸው።
ሊቀመንበሩ ይህን ያሉት ዛሬ ቅዳሜ ጷጉሜ 5፤ 2014 በትዊተር ገጻቸው ባሳፈሩት መልዕክት ነው። ከቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን በፎቶዎች አስደግፈው የገለጹት ማህማት፤ በእርሳቸው ላይ አሁንም “ሙሉ እምነት እንዳላቸው” አስታውቀዋል።
Tweet

I received the AU High Rep for the Horn, H.E. President
Olusegun Obasanjo whose mandate has been
extended.I reiterated my full confidence in him &
encouraged his continued engagement with both
parties & intl actors to work towards peace &
reconciliation in Ethiopia & the region.
African Union and African Union Political Affairs Peace and Security
549 Retweets 120 Quote Tweets 1,091 Likes
ከኦባሳንጆ ጋር በነበራቸው ቆይታም፤ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሰላም እና እርቅ ይመጣ ዘንድ ከሁሉም ወገኖች እና ከዓለም አቀፉ ማህብረሰብ ጋር እያከናወኗቸው ያሏቸውን ስራዎች እንዲቀጥሉ እንዳበረታቷቸው ማህማት በትዊተር መልዕክታቸው አስፍረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ እንዲሆኑ የሾሟቸው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ነበር።
ኦባሳንጆ የልዩ ልዑክ ኃላፊነቱን ከተረከቡ በኋላ የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት በሰላም ለመፍታት ወደ ትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ ጭምር በተደጋጋሚ በመጓዝ የበኩላቸውን ጥረቶችን ሲያደርጉ ቆይተዋል። የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑኩ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ የተቀሰቀሰውን ጦርነት በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት “ዘገምተኛ” ቢሆንም በተፈላሚ ወገኖች መካከል የተኩስ ማቆም ስምምነት የመድረስ ተስፋ እንዳለ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።
የ85 ዓመቱ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ይህን ካስታወቁ በኋላ በተከተሉት ወራት ግን የትግራይ ተፋላሚ ኃይሎች በእርሳቸው የአሸማጋይነት ሚና ላይ ተደጋጋሚ ቅሬታ እና ተቃውሞ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። በትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ተፈርሞ ባለፈው ሰኔ ወር መጀመሪያ ለዓለም አቀፉ ማህብረሰብ የተሰራጨ ደብዳቤ፤ ኦቦሳንጆ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ቅርበት አላቸው በሚል የገለልተኝነት ጥያቄን ማንሳቱ ይታወሳል።
Tweet

Tigray External Affairs Office
An open letter from the President of Tigray on the
position of the government of Tigray with respect to
peace talks @reda_getachew @ProfKindeya
1,387 Retweets 101 Quote Tweets 1,159 Lik
በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በኦባሳንጆ አሸማጋይነት ድርድር ከሚደረግ ይልቅ፤ በወቅቱ በስልጣናቸው ላይ በነበሩት የኬንያው ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ አማካኝነት እንዲደረግ የትግራይ ኃይሎች ፍላጎታቸውን አስታውቀው ነበር። በኬንያ መንግስት አመቻችነት በሚደረገው በዚህ ድርድር ላይም፤ ዩናይትድ ስቴትስ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የተባበሩት መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረት ተሳታፊ እንዲሆኑ እንደሚፈልጉ የትግራይ ኃይሎች በሰኔው ደብዳቤያቸው ጠቁመዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
