September 10, 2022

በትግራይ ተፋላሚ ኃይሎች ተደጋጋሚ ቅሬታ የሚቀርብባቸው የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፤ በአፍሪካ ህብረት  በኩል የተሰጣቸው የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ኃላፊነት ተራዘመላቸው። የኦባሳንጆ የልዩ ልዑክ ሹመት መራዘሙን የገለጹት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማህማት ናቸው። 

ሊቀመንበሩ ይህን ያሉት ዛሬ ቅዳሜ ጷጉሜ 5፤ 2014 በትዊተር ገጻቸው ባሳፈሩት መልዕክት ነው። ከቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ጋር ተገናኝተው መነጋገራቸውን በፎቶዎች አስደግፈው የገለጹት ማህማት፤ በእርሳቸው ላይ አሁንም “ሙሉ እምነት እንዳላቸው” አስታውቀዋል።

Tweet

Moussa Faki Mahama

@AUC_MoussaFaki

I received the AU High Rep for the Horn, H.E. President

Olusegun Obasanjo whose mandate has been

extended.I reiterated my full confidence in him &

encouraged his continued engagement with both

parties & intl actors to work towards peace &

reconciliation in Ethiopia & the region.

Image

Image

Image

African Union and African Union Political Affairs Peace and Security

·Twitter for Android

549 Retweets 120 Quote Tweets 1,091 Likes

ከኦባሳንጆ ጋር በነበራቸው ቆይታም፤ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ሰላም እና እርቅ ይመጣ ዘንድ ከሁሉም ወገኖች እና ከዓለም አቀፉ ማህብረሰብ ጋር እያከናወኗቸው ያሏቸውን ስራዎች እንዲቀጥሉ እንዳበረታቷቸው ማህማት በትዊተር መልዕክታቸው አስፍረዋል። የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ እንዲሆኑ የሾሟቸው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር አጋማሽ ላይ ነበር። 

ኦባሳንጆ የልዩ ልዑክ ኃላፊነቱን ከተረከቡ በኋላ የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት በሰላም ለመፍታት ወደ ትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቐለ ጭምር በተደጋጋሚ በመጓዝ የበኩላቸውን ጥረቶችን ሲያደርጉ ቆይተዋል። የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑኩ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ የተቀሰቀሰውን ጦርነት በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት “ዘገምተኛ” ቢሆንም በተፈላሚ ወገኖች መካከል የተኩስ ማቆም ስምምነት የመድረስ ተስፋ እንዳለ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር። 

የ85 ዓመቱ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ይህን ካስታወቁ በኋላ በተከተሉት ወራት ግን የትግራይ ተፋላሚ ኃይሎች በእርሳቸው የአሸማጋይነት ሚና ላይ ተደጋጋሚ ቅሬታ እና ተቃውሞ ሲያቀርቡ ቆይተዋል። በትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ተፈርሞ ባለፈው ሰኔ ወር መጀመሪያ ለዓለም አቀፉ ማህብረሰብ የተሰራጨ ደብዳቤ፤ ኦቦሳንጆ ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ቅርበት አላቸው በሚል የገለልተኝነት ጥያቄን ማንሳቱ ይታወሳል።

Tweet

Tigray External Affairs Office

@TigrayEAO

An open letter from the President of Tigray on the

position of the government of Tigray with respect to

peace talks @reda_getachew @ProfKindeya

Image

Image

·Twitter for iPhone

1,387 Retweets 101 Quote Tweets 1,159 Lik

በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር በኦባሳንጆ አሸማጋይነት ድርድር ከሚደረግ ይልቅ፤ በወቅቱ በስልጣናቸው ላይ በነበሩት የኬንያው ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ አማካኝነት እንዲደረግ የትግራይ ኃይሎች ፍላጎታቸውን አስታውቀው ነበር። በኬንያ መንግስት አመቻችነት በሚደረገው በዚህ ድርድር ላይም፤ ዩናይትድ ስቴትስ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ የተባበሩት መንግስታት እና የአፍሪካ ህብረት ተሳታፊ እንዲሆኑ እንደሚፈልጉ የትግራይ ኃይሎች በሰኔው ደብዳቤያቸው ጠቁመዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)