

· ስለኤፍራጥስ_ወንዝ_መድረቅ_መጽሐፍ_ቅዱስ_ምን_ይላል? መድረቁስ ምኑን ያመለክታል?=======================
ይህ ወንዝ በመካከለኛው ምስራቅ ረዠሙና ትልቁ ወንዝ ሲሆን ርዝመቱ 2,800 km፣ የምንጭ ከፍታ ደግሞ 4,500 m አማካይ ይሆናል።
ወንዙ እንደደረቀ አለም አቀፍ ሚድያዎች ሰሞኑ እንደዘገቡ ይታወቃል።
ከዚህ በጨማሪ በአዲስ ክዳን ውስጥ (የዮሐንስ ራእይ 9 ፡14)
በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ የታሰሩ አራት ገዳይ መላእክት እንዳሉና በመጨረሻው ዘመን እንደምፈቱ ተጽፎዋል።
ስፈቱም ሰዎችን 1/3 እንደምገድሉ በዮሐንስ ራእይ 9 ፡15ላይ ተፅፎ እናገኛለን። የ
14፤ መለከትም ያለውን ስድስተኛውን መልአክ። በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ የታሰሩትን አራቱን መላእክት ፍታቸው አለው።
ስለወንዙ መድረቅና ለምን እንደምደርቅ(የዮሐንስ ራእይ 16 )
12፤ ስድስተኛውም ጽዋውን በታላቁ ወንዝ በኤፍራጥስ ላይ አፈሰሰ፤ ከፀሐይም መውጫ ለሚመጡ ነገሥታት መንገድ እንዲሰናዳላቸው ውኃው ደረቀ።
1.የአለም መጨረሻ እየደረሰ እንደሆነ አመላካች ነው።
ራዕ 9:18 (ከአፋቸውም በወጡት በእሳቱና በጢሱ በዲኑም በእነዚህ ሦስት መቅሰፍቶች የሰዎቹ ሲሶ ተገደለ።)
የዮሐንስ ራእይ 16 ፡6 ላይ የተፃፈው ቃል ከአሁን በኋላ ትንቢት ሳይሆን እውነት ነው።
