· 

May be an image of 1 person and standing

Belay Bekele Weya  · ለ “አባ” ለአባማ “አባ ጨጓሬ”ም አባ ነው

(በላይ በቀለ ወያ)

..ሳያዩ የሚያምኑን ፣ አይተህ ተጠራጠር

ተአምር አየሁ አትበል

ጋንን ያህል ነገር ፣ ሲደገፍ በጠጠር

ይልቅ ተአምር ስራ

ከሚታይ መልስ ላይ ፣ጥያቄ በመፍጠር።

ሁሉንም አትመን ፣ ግን ሁሉን ተጠንቀቅ

ቤትህ በሰማይ ነው

ብሎ ለሰበከህ ፣ ምድርህን አትልቀቅ።

ከስጋ ፍላጎት

አርቀህ ስቀለው ፣ የነፍስያህን ልክ

የቄስ ቃል ስታምን ፣ ቄሱን ግን አታምልክ።

ሁሉ ካህን አይደል

አስሮ የሚፈታ ፣ እየፈታ ሚያስር

ስንቶች በካህን ለምድ

እባብ ደብቀዋል፣ ከጥምጣማቸው ስር።