ከዚህ በፊት ባቀረብኩት ትርክት ላይ ራሴን እንዳስተዋወቅሁት ኃይሉ አንተነህ ተብዬ ልጠቀስ እችላለሁ::
በውቅቱ የጫረብኝ ክፉ ስሜት ልጅቱ ቆንጅዬና ተግባቢ ልጅ ስለነበረች ምልባት እንዲህ እየመጡ አጨዋውተዋት የሚሄዱት ወንዶች ቢበዛ በፍትወት ስሜት ፈልገዋት ሊሆን ይችል ይሆናል የሚል ሲሆን ለዚህም ከቶውን ግድ የሌለኝ ጉዳይ ነበር:: በወቅቱ አንድም ልጅ ነኛ፣ ሲበዛ ደግሞ ለትግል የመነንኩ ነበርኩ:: የእኔ ዋናው ተልእኮ ልጅቱን ምክንያት አድጌ ወደ ጦር ሰፈሩ ካምፕ መግባት መቻሌና ለድርጅቱ እንቅስቃሴ ያመች ዘንድ ሁኔታዎችን በመቃኘት ማመቻቸት ብቻና ብቻ ነበር::