VOA Amharic 

ጁላይ 12, 2023


የኤርትራው ፕሬዚዳንት ስለ ሱዳን ሰላም በሚመክረው ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ካይሮ ገብተዋል
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ስለ ሱዳን ሰላም በሚመክረው ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ካይሮ ገብተዋል

የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈ ወርቂ፣ በሱዳን ግጭት ጉዳይ፣ ነገ በግብጽ ለሚደረገው የጎረቤት ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ካይሮ ገብተዋል።

ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈ ወርቂ፣ ሌሎች ባለሥልጣኖቻቸውንም ይዘው እንደተጓዙ፣ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረ መስቀል በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል።

Tweet

Yemane G. Meskel

@hawelti

President Isaias Afwerki and his delegation arrive in Cairo to participate

in the Summit of Heads of State and Government of countries

neighbouring the Sudan which will be convened tomorrow.

Image

Image

· 20.6K Views

537 Retweets 25 Quotes 721 Likes 10 Bookmarks

ባለፈው ሰኞ፣ አራት አባላት ያሉት የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ቡድን(IGAD)፣ በሱዳኑ ግጭት ላይ ለመነጋገር በዐዲስ አበባ ተስብሰቦ የነበረ ሲኾን፣ ሁለቱም ተፋላሚ ጄኔራሎች በስብሰባው ላይ ሳይገኙ ቀርተዋል።

በዐዲስ አበባ የተካሔደውን ስብሰባ፣ ኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ መምራት የለባቸውም፤ ለተቃዋሚው ኃይል ያደላሉ፤”

“በዐዲስ አበባ የተካሔደውን ስብሰባ፣ ኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ መምራት የለባቸውም፤ ለተቃዋሚው ኃይል ያደላሉ፤” በሚል፣ የሱዳን መንግሥት በስብሰባው እንደማይሳተፍ አስታውቆ ነበር። ተቀናቃኙ የፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ኃይሉ፣ አንድ ተወካዩ በስብሰባው ላይ እንዲገኝ ወደ ዐዲስ አበባ ልኮ ነበር።

በአሜሪካ እና በሳዑዲ አረቢያ አሸማጋይነት፣ ሁለቱን ወገኖች ስምምነት ላይ ለማድረስ፣ ባለፈው ወር ለሳምንታት ሲደረግ የነበረው ጥረት ሳይሳካ መቅረቱ ይታወሳል።