ራሳቸውን ለመምራት የተሳናቸውን የአእምሮ ሕሙማን፣ ከተለያዩ ሥፍራዎች አንሥቶ የሚረዳቸው፣ “ጌርጌሴኖን የአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማኅበር” ፣ በዛሬው የጤና ዝግጅታችን የምንቃኘው ማዕከል ነው፡፡
በበጎ ፈቃደኛው አቶ መለሰ አየለ የተቋቋመው ጌርጌሴኖን፣ እስከ አሁን፣ ከአንድ ሺሕ በላይ የአእምሮ ሕሙማንን ከጎዳና ላይ ሲያነሣ፣ ከእነርሱም ብዙዎቹ፣ ከሕመማቸው ድነውና አገግመው ማኅበረሰቡን እንዲቀላቀሉ…
