VOA Amharic 

ጁላይ 28, 2023


A view shows motorists driving along a street in Addis Ababa
A view shows motorists driving along a street in Addis Ababa

ኢትዮጵያ ለትምህርት እና ለሕፃናት ምገባ የሚውል፣ 400 ሚሊዮን ዶላር፣ በርዳታ እና በብድር መልክ፣ ከዓለም ባንክ ልታገኝ እንደኾነ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ትላንት ይፋ አድርጓል።

ከድጋፍ ገንዘቡ 350 ሚሊዮን ዶላር በርዳታ እና 50 ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ በብድር እንደተገኘ፣ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ይፋ ያደረገው መግለጫ አመልክቷል።

ገንዘቡ፣ “የልጃገረዶች እና የአዳጊ ልጆችን የትምህርት ውጤት እና አመጋገብ ለማሻሻል፤ የአገልግሎቶችን አቀራረብ እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር፣ በግጭት እና በድርቅ የተጎዱ፣ እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ የሚገኙባቸውን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ጥቅም ላይ ይውላል፤” ሲል መግለጫው አብራርቷል።

Tweet

The Ministry of Foreign Affairs of #Ethiopia 

@mfaethiopia

The Government of Ethiopia and the @WorldBank inked today a

financing agreement to disburse USD 405 million to boost human

capital development in Ethiopia, especially, in the fields of education,

healthcare and job creation for the youth.

H.E. Demeke Mekonnen Hassen, Deputy Prime Minister and Foreign Minister of Ethiopia sharing the stage with Tanzanian President, H.E. Samia Suluhu Hassan, during a panel discussion on education at "The African Human Capital Heads of State Summit" at the Julius Nyerere International Convention Centre (JNIC) in Dar es Salaam, Tanzania circa 26 July 2023.

Photo: @mfaethiopia

ALT

· 19.7K Views

84 Retweets 6 Quotes 237 Likes 2 Bookmarks

ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያጋጠማት ኢትዮጵያ፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ለሁለት ዓመታት የዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እና ድርቅ፣ እንዲሁም የጎርፍ አደጋ እና የአንበጣ ወረርሽኝ በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ያደረሷቸው ጉዳቶች ጫና አሁንም ድረስ እንደ ጎላ ነው።