ጁላይ 28, 2023

ኢትዮጵያ ለትምህርት እና ለሕፃናት ምገባ የሚውል፣ 400 ሚሊዮን ዶላር፣ በርዳታ እና በብድር መልክ፣ ከዓለም ባንክ ልታገኝ እንደኾነ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ትላንት ይፋ አድርጓል።
ከድጋፍ ገንዘቡ 350 ሚሊዮን ዶላር በርዳታ እና 50 ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ በብድር እንደተገኘ፣ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ይፋ ያደረገው መግለጫ አመልክቷል።
ገንዘቡ፣ “የልጃገረዶች እና የአዳጊ ልጆችን የትምህርት ውጤት እና አመጋገብ ለማሻሻል፤ የአገልግሎቶችን አቀራረብ እና ተጠያቂነትን ለማጠናከር፣ በግጭት እና በድርቅ የተጎዱ፣ እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስደተኛ የሚገኙባቸውን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ጥቅም ላይ ይውላል፤” ሲል መግለጫው አብራርቷል።
Tweet

The Ministry of Foreign Affairs of #Ethiopia
The Government of Ethiopia and the @WorldBank inked today a
financing agreement to disburse USD 405 million to boost human
capital development in Ethiopia, especially, in the fields of education,
healthcare and job creation for the youth.
ALT
84 Retweets 6 Quotes 237 Likes 2 Bookmarks
ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያጋጠማት ኢትዮጵያ፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ ለሁለት ዓመታት የዘለቀው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት እና ድርቅ፣ እንዲሁም የጎርፍ አደጋ እና የአንበጣ ወረርሽኝ በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ያደረሷቸው ጉዳቶች ጫና አሁንም ድረስ እንደ ጎላ ነው።